የአውሮፓ ሕብረት መሪዎችና አጀንዳዎቻቸው
ዓርብ፣ ሰኔ 20 2006ማስታወቂያ
በሆነችው ከተማ በመሰብሰብ ፣ በጦርነቱ ያለቁትን በልዩ ሥነ ሥርዓት አስበዋቸዋል።ከዚያም ወደ ብራሰልስ ተመልሰው ዛሬ እስከ ምሽት ደረስ ፣ በሚቀጥሉት 5 ዓመታት ቅድሚያ ሊሰጣቸው ይገባል ባሏቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል።ብሪታንያ ብትቃወመም፣ የቀድሞውን የላክሰምበርግ ጠ/ሚንስትር ዣን ክሎድ ዩንከርን የኮሚሽኑ አዲስ ተሿሚ ይሆኑ ዘንድ ሰይመዋል። አወዛጋቢውና ለዩክሬይን ቀውስ ሰበብ የሆነው የሕብረቱና የዩክሬይን ነጻ የንግድ ስምምነት በጉባዔው ፊት ተፈርሟል። ይህ የዩክሬኑን የፖለቲካ ፍጥጫ በማርገብ ፤ አገሪቱ አንድነቷን ጠብቃ እንድትቀጥል የሚረዳ የመሆን ያለመሆኑ ጉዳይም ማነጋገሩ አልቀረም ። የስደተኞች ጉዳይ ሌላው ዐቢይ ርእስ ነበር።
ገበያው ንጉሤ
ተክሌ የኋላ
አርያም ተክሌ