የአውሮፓ የስደተኞች ቀውስ
ረቡዕ፣ የካቲት 25 2012![Migranten an der griechisch-türkischen Grenze](https://static.dw.com/image/52621244_800.webp)
ማስታወቂያ
ቱርክ የአውሮፓ ድንበሯን ከከፈተች በኋላ ሶማሊያውያንን ጨምሮ በሺሕዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች ወደ ግሪክ ለማቆረጥ መንገድ በማፈላለግ ላይ ናቸው። ስደተኞቹ በቱርክ ድንበር የሚፈሰውን የኢቭሮስ ወንዝ በእግር ለማቋረጥ ሙከራ እያደረጉ መሆኑን አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል።
የኢቭሮስ ረግረጋማ ሥፍራን ለማቋረጥ የሞከሩ 1,000 ገደማ ስደተኞች ማገዳቸውን የግሪክ ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። ወደ አውሮፓ ለመሻገር ከሚሞክሩት መካከል የአፍጋኒስታን፣ ፓኪስታን፣ ሞሮኮ፣ ባንግላዴሽ፣ ሶማሊያ እና ማሊ ዜጎች ይገኙበታል።
በኢድሊብ ከሶርያ ኃይሎች ግብግብ የገጠመችው ቱርክ በአውሮፓ ላይ ጫና ለማሳደር ድንበሯን በግዛቷ ላስጠለለቻቸው ስደተኞች እንደምትከፍት አስታውቃለች። ከ3.5 ሚሊዮን በላይ የሶርያ ስደተኞች ያስጠለለችው የቱርክ ፕሬዝዳንት ረቺብ ጣይብ ኤርዶኻን ከአውሮፓ ከፍ ያለ ድጋፍ ጠይቀዋል።
ገበያው ንጉሴ
ሸዋዬ ለገሠ