የአየር በረራና ከውጭ የሚያጋጥሙት እክሎች፣20 ጥር 2001ረቡዕ፣ ጥር 20 2001በየብስ ፣ አውቶሞቢሎችና ባቡሮች አደጋ በማያጋጥምበት ሁኔታ ይሽከረከሩ ዘንድ የትራፊክ ህግ መመሪያ ሆኖ እንደሚያገላግላቸው የታወቀ ነው። የንግድና የጦር መርከቦች ም ቢሆኑ በጭፍኑ አይደለም፣ በግዙፎቹ ውቅያኖሶች ላይ የሚቀዝፉት።ማገናኛዉን ኮፒ አድርግለአኤሮፕላን በራራ እንቅፋት የሚሆኑ አእዋፍ፣ምስል APማስታወቂያበአየር ላይ የሚበሩ ጥያራዎችም በአገር አቀፍና ዓለም-አቀፍ መመሪያ ደንብ፣ በራዳር አማካኝነት መስመራቸውን (ከፍታንና ዝቅታን ይጨምራል)ጠብቀዉ ስለሚበሩ፣ በአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ወይም በአብራሪዎች ስህተት ካልተፈጠረ በስተቀር የግጭት አደጋ አያጋጥምም።