1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የአይቮሪ ኮስት ጠቅላይ ምኒስትር አማዱ ጎን ኩሉባሊ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

01:54

This browser does not support the video element.

ሐሙስ፣ ሐምሌ 2 2012

የአይቮሪ ኮስት ጠቅላይ ምኒስትር አማዱ ጎን ኩሉባሊ በድንገት ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። ጠቅላይ ምኒስትሩ ከአገራቸው ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር ስብሰባ ላይ ሳሉ ሕመም ተሰምቷቸው ረቡዕ ሐምሌ 2 ቀን 2012 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

የአይቮሪ ኮስት ጠቅላይ ምኒስትር አማዱ ጎን ኩሉባሊ በድንገት ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።ጠቅላይ ምኒስትሩ ከአገራቸው ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር ስብሰባ ላይ ሳሉ ሕመም ተሰምቷቸው ረቡዕ ሐምሌ 2 ቀን 2012 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። ከሁለት ወራት ሕክምና በኋላ ከፈረንሳይ የተመለሱት በቅርቡ ነበር።  ጠቅላይ ምኒስትሩ ለመጪው ምርጫ ገዢውን ፓርቲ ወክለው ለፕሬዝዳንትነት ሊወዳደሩ ታጭተው ነበር። ፕሬዝዳንት አላሳን ዋታራን ይተካሉ ተብለው ይጠበቁ የነበሩት የ61 አመቱ ኩሉባሊ ምን ለሞት እንዳበቃቸው የታወቀ ነገር የለም። 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW