የአዲስ አበባ ነዋሪ ተቃዉሞና ጥያቄ
ሰኞ፣ መስከረም 7 2011ማስታወቂያ
ለጥቃቱ እጃቸው አለበት የተባሉ ከ600 መቶ የሚበልጡ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄኔራል ዘይኑ ጀማል ከጥቂት ሰዓታት በፊት በሰጡት መግለጫ አሳዉቀዋል። ግጭትና ግድያዉ አገሪትዋ የጀመረችዉ ለውጥ እንዳይሳካ ለማድረግ ሰፊ በሆነ እቅድ ተዘጋጅቶ ታስቦበት የተከናወነ እንደሆነና ግን የጸጥታ ኃይሎች ባደረጉት ርብርብ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር መዋሉን ጄኔራል ዘይኑ ጀማል ተናግረዋል። ከአለም ዜና እንደተከታተላችሁት በሳምንቱ መጨረሻ በቡራዩ አካባቢና በአንድ አንድ የአዲስ አበባ ከተማ አካባቢዎች በተከሰተ ብሔር ተኮር ግጭት ከሀያ የሚበልጥ ሰው መሞቱን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታዉቆአል። የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አለማየሁ እጅጉ በግጭቱ 23 ሰው መሞቱን ቢያረጋግጡም፣ የሟች ቁጥር ከፍ ሊል እንደሚችል ነዉ የተገለፀዉ።
ጌታቸዉ ተድላ
አዜብ ታደሰ
ነጋሽ መሀመድ