የአዲስ አበባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት መግለጫ
ማክሰኞ፣ ኅዳር 7 2014![Äthiopien Addis Abeba | Politiker](https://static.dw.com/image/59839517_800.webp)
ማስታወቂያ
የአዲስ አበባ ሕዝብ ራሱንና አገሩን እንዲጠብቅ መንግሥት እንዲያስታጥቀው ተጠየቀ። ከኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት እውቅና አለው የተባለ እና በአዲስ አባባ ከተማ ምርጫ ላይ የተሳተፉ ፖርቲዎችን ያቀፈ የፖለቲካ ፓርቲዎች ስብስብ አቅም ያለው የአዲስ አበባ ነዋሪ ወደ ጦር ግንባር ለመሄድ እንዲዘጋጅ ሌላው ደግሞ በገንዘብ እንዲደግፍ ጠይቋል። ኢትዮጵያ አሁን የገጠማት ችግር እጅግ ፈታኝ ነው ያለው የአዲስ አበባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ኢትዮጵያ አሻንጉሊት መንግሥት አያስፈልጋትም በማለት ከሰሞኑ አሜሪካ ውስጥ መንግሥትን በኃይል ጭምር ለመጣል የተፈራረሙትን ኃይሎች ተግባር ኮንኗል።
ሰለሞን ሙጬ
አዜብ ታደሰ
ኂሩት መለሰ