1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የአዲስ ዓመት ተስፋ በትግራይ

ሚሊዮን ኃይለ-ሥላሴ
ሐሙስ፣ መስከረም 1 2018

የተገባደደው 2017 ዓመተ ምህረት በትግራይ ከፍተኛ ፖለቲካዊ ቀውሶች፣ የፀጥታ ስጋቶች፣ ክፍፍል (የህወሓትና የታጣቂዎች) የታየበት ዓመት ሆኖ አልፏል። ለዓመታት ክልሉን የመራው ህወሓት ለሁለት መከፈሉ ተከትሎ ከፍተኛ ፖለቲካዊ እና የድህንነት ስጋት ተፈጥሮ ቆይቷል። በእነዚህ እና ሌሎች ምክንያቶች ዜጎች ዓመቱን በጦርነት ስጋት ውስጥ አሳልፈውታል።

መቀለ ከተማ ፤ በአዲስ ዓመት መስከረም 1 ቀን 2018
መቀለ ከተማ ፤ በአዲስ ዓመት መስከረም 1 ቀን 2018 ምስል፦ Million Hailesilassie/DW

የአዲስ ዓመት ተስፋ በትግራይ

This browser does not support the audio element.

የአዲስ ዓመት ተስፋ በትግራይ 

የተገባደደው 2017 ዓመተ ምህረት በትግራይ ከፍተኛ ፖለቲካዊ ቀውሶች፣ የፀጥታ ስጋቶች፣ ክፍፍል (የህወሓት እና የታጣቂዎች) የታየበት ዓመት ሆኖ አልፏል። ለዓመታት ክልሉን የመራው ህወሓት ለሁለት መከፈሉ ተከትሎ ከፍተኛ ፖለቲካዊ እና የድህንነት ስጋት ተፈጥሮ ቆይቷል። በእነዚህ እና ሌሎች ምክንያቶች ዜጎች ዓመቱን በጦርነት ስጋት ውስጥ አሳልፈውታል። ከትግራይ ያነጋገርናቸው ነዋሪዎች በአዲሱ ዓመት ሰላም፣ የተረጋጋ ፖለቲካዊ ሁኔታ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ መነቃቃት ይመኛሉ።  በትግራይ ደቡባዊ ዞን እየበረታ የመጣዉ ፖለቲካዊ አለመረጋጋት

የተጠናቀቀ 2017 ዓመተምህረት በትግራይ በርካታ የሚባሉ ታሪካዊ ሁነቶች የታዩበት፣ ከምንም በላይ ደግሞ በፖለቲካዊ ውጥረት ውስጥ ተሁኖ ያለፈ ዓመት ተደርጎ በበርካቶች ይታወሳል። የሃምሳ ዓመት ዕድሜ ያለው ህወሓት በውስጡ የተፈጠረው ክፍፍል ተከትሎ፥ የዚሁ ክፍፍል ተቀጥያ የሆኑ ልዩነቶች በሲቪል እና ወታደራዊ ተቋማት የተከሰተበት ዓመት ነበር፥ የተገባደደው 2017 ዓመተምህረት። ህወሓት እና የፌደራል መንግስት ወደ ሌላ ዙር ፍጥጫ እንዳይገቡም ከፍተኛ ስጋት በበርካቶች ተፈጥሮ ዓመቱ አልፏል። ከመቐለ እና ሌላ የትግራይ አካባቢዎች ያነጋገርናቸው ነዋሪዎች የሚናገሩትም ይህንኑ ነው።

ሚሊዮን ኃይለሥላሴ 

አዜብ ታደሰ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW