የካቢኔ አባላት ሹመት
ማክሰኞ፣ ጥቅምት 22 2009ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የ30 የካቢኔ አባላትን ሹመት ዛሬ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርበው አጸደቁ። ከካቢኔ አባላቱ መካከል 21 ዱ አዳዲስ አባላት ሲሆኑ 9ኙ ደግሞ ነባር አባላት ናቸው ። ከመካከላቸው ሦስት ሴቶች የሚገኙበትን ይህንኑ አዲስ ካቢኔ የኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያጸደቀው በሙሉ ድምፅ ነው። ከዚህ ቀደም በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ በክላስተር የማስፈፀም እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ የሚባሉ ቦታዎች ሙሉ በሙሉ መቅረታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም አስታውቀዋል። ዝርዝሩን የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ልኮልናል ።
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
ኂሩት መለሰ
አዜብ ታደሰ