1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የአፈር ለምነት ጥናት በኢትዮጵያ

ማክሰኞ፣ ታኅሣሥ 26 2008

አስር የአፍሪቃ ሃገራት ወደ31 ሚሊየን ሄክታር የተጎሳቆለና የተራቆተ መሬት እስከጎርጎሪዮሳዊዉ 2030ዓ,ም ምርታማ መሆን እንዲችል የመጠበቅ ሥራ ለመሥራት መዘጋጀታቸዉ ከአራት ሳምንታት በፊት ነዉ የተሰማዉ። በዚህ ዘመቻም ኢትዮጵያን ጨምሮ ኬንያ ሩዋንዳ፣ ዩጋንዳ፣ ማላዊ ኒዠር እና ሌሎች አምስት ሃገራት ተሳታፊ ናቸዉ።

Bauer bei der Arbeit in Äthiopien
ምስል፦ AP

የአፈር ለምነት ጥናት በኢትዮጵያ

This browser does not support the audio element.

ኢትዮጵያ በዓይነቱ የተለየ የአፈር ለምነት ጥናት ማካሄዷን መረጃዎች ያመለክታሉ። እንዲህ ያለዉ ጥናት በአፍሪቃ ሲካሄድም ኢትዮጵያ የመጀመሪያዋ መሆኗም ተገልጿል። በጉዳዩ ላይ ያነጋገርናቸዉ የዘርፉ ባለሙያ እንደሚሉት ከሆነም ከመላዉ ዓለምም ቢሆን ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቅ በመሆኑ ብዙዎች ይህን ጥናት ለማካሄድ አልደፈሩም። በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ የሰጡን የዘርፉ ባለሙያ ፕሮፌሰር ተካልኝ ማሞ አገራዊ የአፈር ለምነት ዳሰሳ ጥናት መርሃ ግብር ኃላፊ ናቸዉ። ፕሮፌሰሩ ለዶቼ ቬለ እንደገለፁት ኢትዮጵያ ላለፉት አራት ዓመታት በ495 ወረዳዎች አገራዊ የአፈር ለምነት ዳሰሳ ጥናት አካሂዳለች። በዚህ የዳሰሳ ጥናትም በየአካባቢዉ የሚገኘዉ አፈር የትኛዉ ንጥረ ነገር እንደጎደለዉ ለመገንዘብ ተችሏል። ጥናቱ የሰብል ምርትና ምርታማነትን በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ እና እያሽቆለቆለ የመጣዉን የአፈር ለምነት ይዞታም ለማሻሻል ያለመ ነዉ። የዳሰሳ ጥናቱ ምን ምንን አካቷል? በምግብ እጥረት ችግር ለሚጎዳዉ ወገንስ የሚያመጣዉ ፋይዳ ምን ይሆን? ዝርዝሩን ከድምጽ ዘገባዉ ያገኙታል።

እርከን በኮንሶ አካባቢምስል፦ by-nc-sa/Terri O'Sullivan

ሸዋዬ ለገሠ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW