የአፍሪቃዉ ህብረት እና ሊቢያ
ሰኞ፣ ነሐሴ 23 2003ማስታወቂያ
በአንድ በኩል አንዳንድ የአፍሪቃ አገራት በሊቢያ የሚቋቋመዉ የሽግግር መንግስት የጋዳፊን ወገኖችንም ያካተተ መሆን አለበት ሲሉ በሌላ በኩል እንደ ኢትዮጽያ ናይጀርያ ሩዋንዳ የመሳሰሉ አገሮች ከስብሰባዉ ዋዜማ ጀምሮ ለሊቢያዉ የሽግግር ምክርቤት እዉቅና በመስጠታቸዉ በህብረቱ ልዪነት ተፈጥሮአል። ስብሰባዉን የመሩት የደቡብ አፍሪቃዉ ፕሪዝደንት ጃኮብ ዙማ ለሊቢያዉ የሽግግር ምክር ቤት እዉቅና እንዳይሰጥ በጥብቅ ሲከራከሩም ታይቶአል። የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ታደሰ እንግዳዉ ፕሪዝደንት ጃኮብ ዙማን አነጋግሮ ዘገባ ልኮልናል።
ታደሰ እንግዳዉ
አዜብ ታደሰ
አርያም ተክሌ