1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአፍሪቃ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን

ማክሰኞ፣ ግንቦት 10 2002

የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን ስራውን ጀመረ

ምስል AP

በቀድሞው የቦትስዋና ፕሬዝዳንት የሚመራውና 60 አባላት ያሉት የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን ትላንት በይፋ ስራውን መጀመሩን የቡድኑ መሪ ሰር ኬቱሚሌ ማሲሬ በተለይ ለዶቸ ቬሌ ገልጸዋል። የታዛቢው ቡድን ከአምባሳደሮች፤ ከብሄራዊ ምክር ቤት አባላት፣ ከፓን አፍሪካ ፓርላሜንት እንዲሁም ከተለያዩ የአፍሪካ ሃገራት ከተጋበዙ ታዋቂ ግለሰቦች ኀተወጣጡ አባላትን ያቀፈ ነው። የቡድኑ መሪ የአባላቱ ቁጥር ከምርጫ ጣቢያዎች ቁጥር አንጻር በቂ ናቸው ለሚለው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ በተመረጡና ለግምገማቸው ውጤታማ መሆን አስተዋጽኦ በሚኖራቸው የተወሰኑ የምርጫ ጣቢያዎች እንደሚሰማሩ ገልጸዋል።

መሳይ መኮንን

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW