የኢራን እና ስዑዲ ዓረቢያ ውዝግብ
ረቡዕ፣ ታኅሣሥ 27 2008ማስታወቂያ
በሞት መቅጣቷ የፈጠረው ቁጣ ነገሩን እንዳጦዘው ተገልጧል።የሼሕ ኒምር አል ኒምር በስዑዲ ዓረቢያ በሞት መቀጣት የኢራንን ሕዝብ አስቆጥቶ አደባባይ እንዳስወጣው ይታወሳል። ያም ብቻ አይደለም ሕዝቡ በመዲናዪቱ ቴሕራን የሚገኘው የስዑዲ አረቢያ ኤምባሲ ቅጥር ግቢን በእሳት መለኮሱ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቱ እንዲቋረጥ ሰበብ ተደርጎ ይወሰዳል። በእርግጥ በስዑዲ ዓረቢያ እና ኢራን መካከል በአካባቢው ተሰሚነትን ለማግኘት የሚደረግ ፉክክር ቢኖርም ማለት ነው። የኢራን እና ስዑዲ ዓረቢያ ውጥረትን በተመለከተ የጂዳ ተባባሪ ዘጋቢያችን ነቢዩ ሲራክን በሥልክ አነጋግሬዋለሁ። የሁለቱ ሃገራት ግንኙነት መቋረጥን ተከትሎ የሌሎች ሃገራት ውሳኔ ምን እንደሚመስል በመተንተን ይጀምራል።
ነቢዩ ሲራክ
ማንተጋፍቶት ስለሺ
ነጋሽ መሐመድ