1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢራን እና ስድስቱ ታላላቅ መንግስታት ምክክር

ዓርብ፣ መስከረም 22 2002

ጀርመንን ጨምሮ አምስቱ የመንግስታቱ ድርጅት የጸጥታ ምክር ቤት ቋሚ አባላት አሜሪካ ሩስያ ቻይና እንግሊዝ እንዲሁም ፈረንሳይ፣ በኢራን የኒኩልየር ግንባታ ዙርያ ለመጀመርያ ግዜ በስዊዘርላንድ ጄኔቭ ላይ መምከር የጀመሩ ሲሆን

በስዊዘርላንድ ጄኔቭ በመምከር ላይምስል AP

ዉይይቱ በመግባባት መከናወኑ እና በመቀጠል በቅርቡ እንደገና ዉይይት ለማድረግ መስማማታቸዉ ተዘግቦአል። ከዚሁ ጎን ለጎን ላላፉት 30 አመታት በባላጣነት ይተያዩ የነበሩት የአሜሪካ እና የኢራን መንግስታት ተደረዳሪዎች፣ የተናጠል ዉይይት ማድረጋቸዉ ተጠቁሞአል። ይህም ሆኖ ከኢራን ስለሚጠበቀዉ የኑክልየር ጣብያን ማስፈተሽም ሆነ፣ በቅርቡ ይፋ የሆነዉ የኑክልየር ጣብያ የዉይይቱ ዋንኛ የመነጋገርያ አጀንዳ ይሆናል ተብሎ ቢገመትም፣ በዚህ ረገድ ተደራዳሪዎች ስለደረሱበት ስምምነት ይፋ የወጣ መግለጫ አለመኖሩ ተነግሮአል። ዝርዝሩን የሳዉዲአርብያዉ ወኪላችን ነብዩ ሲራክ ልኮልናል።

ነብዩ ሲራክ ፣ አዜብ ታደሰ፣ አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW