1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮምህዳር ጋዜጠኞች አደጋና ውሳኔ

ረቡዕ፣ ጥቅምት 20 2006

አደጋው ከደረሰባቸው ጋዜጠኛ አንዱ ጌታቸው ወርቁ እንዳስታወቀዉ ለአደጋ የተጋለጡት የተሳፈሩበት ባጃጅ በሞተር ብስኪሌት በመገጨቱ ነዉ።የሃዋሳ ፍርድ ቤት ጉዳዩን ለማየት ሥልጣን የለውም መከሰስ ያለበትም ዋና አዘጋጁ ነው ሲሉ ጋዜጠኞቹ ያቀረቡትን ጥያቄ ዛሬ ከሰዓት ውድቅ አድርጓል።

ምስል DW

ሶስት የኢትዮ ምህዳር ጋዜጠኞች ዛሬ በሃዋሳ ከተማ በደረሰባቸው የግጭት አደጋ መጎዳታቸዉን አስታወቁ ። ጋዜጠኖቹ አደጋው የደረሰባቸው ስለ ሃዋሳ ዩኒቨርስቲ ባወጡት ዘገባ ለቀረበባቸው ክስ የሲዳማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሰጣቸው ቀጠሮ መሰረት ሃዋሳ በተገኙበት ወቅት ነበር።አደጋው ከደረሰባቸው ጋዜጠኛ አንዱ ጌታቸው ወርቁ እንዳስታወቀዉ ለአደጋ የተጋለጡት የተሳፈሩበት ባጃጅ በሞተር ብስኪሌት በመገጨቱ ነዉ።የሃዋሳ ፍርድ ቤት ጉዳዩን ለማየት ሥልጣን የለውም መከሰስ ያለበትም ዋና አዘጋጁ ነው ሲሉ ጋዜጠኞቹ ያቀረቡትን ጥያቄ ዛሬ ከሰዓት ውድቅ ማድረጉን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ከአዲስ አበባ ዘግቧል ።

ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር

ሂሩት መለሰ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW