1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የኢትዮጵያና ሱዳን የድንበር ውዝግብ

ሐሙስ፣ ጥር 6 2013

ሱዳን የኢትዮጵያ ወታደራዊ የጦር ሔሊኮፕተር የሁለቱን አገሮች ድንበር ጥሶ ገብቷል ስትል ትናንት ከሳለች። በተመሳሳይ ቀን ሱዳን ከኢትዮጵያ በምትዋሰንበት ገዳሪፍ ግዛት ዋድ ዛይድ በተባለ አውሮፕላን ማረፊያ የሱዳን ወታደራዊ ሔሊኮፕተር ትናንት ተከስክሷል። አሶሼትድ ፕሬስ እንደዘገበው ሔሊኮፕተሩ የጦር መሳሪያ እና ጥይት የጫነ ነበር።

Karte Sudan Äthiopien EN

የኢትዮጵያ እና ሱዳን የድንበር ውዝግብ

This browser does not support the audio element.

ሱዳን በኢትዮጵያ ሉዓላዊ የድንበር ግዛት ውስጥ ዘልቃ በመግባት ያደረገችው ወረራ ሁለቱ ሀገራት ለረጅም ጊዜ የገነቡትን የወዳጅነት ግንኙነት የበጠሰ፣ ዓለም አቀፍ ሕግንም የጣሰ አደገኛ አካሄድ ነው ተባለ።

የኢትዮጵያን የውስጥ ነባራዊ ሁኔታ እንደምቹ አጋጣሚ በመጠቀም በሱዳን በኩል የተፈፀመው ይህ ድርጊት ለሁለቱ ሀገር ሕዝቦች ዘላቂ መልካም ግንኙነት ብቻ ሳይሆን ለቀጣናውም አስጊ መሆኑንም ዶይቼ ቬለ ያነጋገራቸው ምኁራን ተናግረዋል።

ክስተቱ ኢትዮጵያን ከጀርባ የመውጋት አዝሚሚያ የተስተዋለበት ነው ያሉት ምኁራኑ ችግሩ በሠላም እንዲፈታ የሚደረገው ጥረት እንዲጠናከር፣ ይህ ካልተሳካ ግን አፀፋ መውሰድ እንደሚገባም ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ የሱዳን ጦር ተጠናክሮ ወደ ውስጥ ድንበር ጥሶ እንደገባና ጉዳዩን በዲፕሎማሲ ለመፍታት ትዕግስት መምረጧን ስትገልፅ የሱዳን ጦር በበኩሉ የራሱ የነበረ ቦታን መቆጣጠሩን እንጂ ወደ ኢትዮጵያ ድንበር እንዳልገባ እየተናገረ ነው።

ሰለሞን ሙጬ

ኂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW