በበርካታ የምዕራቡ ዓለም የብዙሀን መገናኛ ስለኢትዮጵያ ሲነሳ፤ ከቱባ ባህልና ታሪኳ ይልቅ፤ ረሀብ፣ እርዛትና የነጣ ድህነቷ ቀድሞ ሲከሰት ነው የሚስተዋለው። በአንፃሩ ሁኔታው እያንገበገበ ሰላም ቢያሳጣቸው፤ የሀገራቸውን በጎ ጎን ለማስተዋወቅ፤ የሲኒማ ጥበባቸውን እንደመሳሪያ አንስተው የሚታገሉም አልታጡም። የዋሽንግተኑ ዘጋቢያችን አበበ ፈለቀ፤ አራት ዘጋቢ ፊልሞችን ቃኝቶ የሚከተለውን አጠናቅሯል።