የኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን የድጋፍ ሰልፍ በፓሪስ
ቅዳሜ፣ ሐምሌ 14 2010![Ethiopians and Eritreans rally](https://static.dw.com/image/44774564_800.webp)
ማስታወቂያ
በዛሬው የፓሪስ የድጋፍ ሰልፍ የኢትዮጵያ እና ኤርትራ አምባሳደሮች ተገኝተዋል። በኢትዮጵያ በኩል በፈረንሳይ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር የሆኑት አሊ ሱሌማይን እና የኤርትራው አቻቸው አምባሳደር ሐና ስምዕን በሰልፉ ላይ ተካፍለዋል። ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን መፈክሮችን አንግበው፤ ባንዲራቸውን እያውለበለቡ ድጋፋቸውን ሲገልጹ ታይተዋል። በፓሪሱ ሰልፍ ከኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን በተጨማሪ የሌሎች አፍሪቃ ሃገራት ዜጎች የየሀገራቸውን ባንዲራ በመያዝ ደስታቸው ገልጸዋል።
ዘጋቢያችን ሃይማኖት ጥሩነህ የፓሪሱን ሰልፍ ተከታትላለች። የሰልፉን ድባብ በተመለከተ ከእርሷ ጋር የተደረገው አጠር ያለ ቃለ ምልልስ ከታች የድምፅ ማዕቀፉ ውስጥ ይገኛል።
ሃይማኖት ጥሩነህ
ተስፋለም ወልደየስ