ኢትዮጵያውያን በፓሪስ ያካሄዱት ውይይት
ዓርብ፣ መጋቢት 27 2011ማስታወቂያ
ፈረንሳይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በተለያዩ ዘርፎች ሀገራቸውን ሊያግዙ እንደሚገባ ተጠየቀ። ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ፓሪስ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በተዘጋጀ ልዩ መድረክ ላይ በፈረንሳይ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጋር በተካሄደ ውይይት ጥሪውን ያስተላለፈው ኤምባሲው፣በበኩሉ ዜጎችን ለመርዳት እና ለማገልገል ዝግጁ መሆኑንን አስታውቋል። በፈረንሳይ አዲሱ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሔኖክ ተፈራ በዚያ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጋር በተዋወቁበት በዚሁ መድረክ ላይ በኤምባሲው ኢትዮጵያውያን ለመሰባሰቢያ እና ለተለያዩ ዝግጅቶች ማካሄጃ የሚጠቀሙበት ቦታ መዘጋጀቱን ተናግረዋል። የፓሪስዋ ወኪላችን ሃይማኖት ጥሩነህ ዝርዝሩን ልካልናለች።
ሃይማኖት ጥሩነህ
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ