1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያውያን ዴያስፖራ ማሕበረሰብ አስተዋጽዖ

ዓርብ፣ ታኅሣሥ 22 2014

አዲሱን የፈረንጆች ዓመት እና የኢትዮጵያ ገናን ምክንያት በማድረግ ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ በመንግስት ጥሪ የተደረገላቸው በርካታ ኢትዮጵያውያን   ወደ አገር ቤት እየመጡ ነው፡፡ ዲያስፖራ ኢትዮጵያውያኑ በሰሜን የአገሪቱ አከባቢዎች በጦርነት የወደሙ መሰረተ ልማቶችን ለመጠገን፤ ይረዳል ያሉትን የህክምና ቁሳቁሶች ይዘው እየመጡ ነው፡፡

Äthiopien medizinische Hilfe
ምስል Seyoum Getu/DW

የመሰረተ ልማቱን ለመጠገን የዲያስፖራው ማህበረሰብ ሚና ጎልቶ እየታየ ነው

This browser does not support the audio element.

አዲሱን የፈረንጆች ዓመት እና የኢትዮጵያ ገናን ምክንያት በማድረግ ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ በመንግስት ጥሪ የተደረገላቸው በርካታ ኢትዮጵያውያን   ወደ አገር ቤት እየመጡ ነው፡፡

ዲያስፖራ ኢትዮጵያውያኑ በሰሜን የአገሪቱ አከባቢዎች በጦርነት የወደሙ መሰረተ ልማቶችን ለመጠገን፤ በተለይም  የህክምና ተቋማት ውድመትን ወደ ነባር ይዞታው ለመመለስ ይረዳል ያሉትን የህክምና ቁሳቁሶች ይዘው እየመጡ ነው፡፡

የአዲስ አበባ ዘጋቢያችን ስዩም ጌቱ ያነጋገራቸው ወደ አዲስ አበባ የተጓዙ አንድ የጀርመን ነዋሪ እንደሚሉት ኢትዮጵያውያን አንድነትን ከፈጠሩ ለአገራቸው በርካታ ቁምነገሮች ሊያበረክቱ ይችላሉ፡፡

ምስል Seyoum Getu/DW

አንድ የዲፕሎማሲ ተንታኝ በፊናቸው እንደሚሉት የኢትዮጵያውያኑ በአገራቸው ጉዳይ የነቃ ተሳትፎ ማድረግ የአገራቸውን ጥቅም ከማስከበር አንጻር ጉልህ ድርሻ ይኖረዋል፡፡

ስዩም ጌቱ 
ታምራት ዲንሳ
ሸዋዬ ለገሰ
 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW