የኢትዮጵያ መንግሥት አዲስ ሕግና ተቃዉሞዉ
ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 30 2001ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ መንግሥት መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን ሥራ እና አሰራር የሚገድብ ሕግ ማዉጣቱ የቀሰቀሰዉ ቁጣና ተቃዉሞ እንደቀጠለ ነዉ።ባለሙያዎችና ሕጉ የሚነካቸዉ ድርጅቶች ተጠሪዎች እንደሚሉት ሕጉ ድርጅቶቹን ብቻ ሳይሆን በድርጅቶቹ ድጋፍ የሚኖረዉን ሕዝብና ሐገሪቱን ጭምር ክፉኛ የሚጎዳ ነዉ።የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ታደሰ እንግዳዉ ያነጋገራቸዉ ባለሙያዎች እንደሚሉት በአዲሱ ሕግ ምክንያት ኢትዮጵያ በአመት ከስድስት መቶ ሚሊዮን እስከ ሁለት ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ ገቢ ታጣለች።