1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የኢትዮጵያ መንግሥት የኢኮኖሚ ዕድገት ዕቅድና የባለሙያ አስተያየት

ሰለሞን ሙጬ
ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 7 2017

የኢትዮጵያ የፕላን እና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ ሰሞኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበትት ለመንግሥት የካቢኔ አባላት የሀገሪቱን የዘጠኝ ወራት የምጣኔ ሐብት የሥራ አፈፃፀም ሲያቀርቡ መንግሥት የያዘውን የ8.4 በመቶ የኡኮኖሚ ዕድገት ውጥን ሊያሳካ የሚችልበት ያሏቸው አመላካቾችን ዘርዝረዋል

አንድ የኤኮኖሚ ባለሙያ ግን የፖለቲካ፣ የባህል፣ የሰላም፣ የሕግ፣ ደንብ እና የአሠራር ኹኔታዎች ለሥራ አመቺ ኹኔታ ሲፈጥሩ የኢኮኖሚ ዕድገት ይኖራል ያሉት ባለሙያው ይህ ካልሆነ ግን "በምኞት ዕድገት የለም" ሲሉ መልሰዋል።
ዶክተር ፍፁም አሰፋ የኢትዮጵያ የፕላን እና ልማት ሚኒስትር።«የኢትዮጵያ ኤኮኖሚ ዘንድሮ በ8.4 በመቶ እንደሚያድግ የሚጠቁሙ ምልክቶች አሉ» ይላሉ።ምስል፦ privat

የኢትዮጵያ መንግሥት የኢኮኖሚ ዕድገት ዕቅድና የባለሙያ አስተያየት

This browser does not support the audio element.

የኢትዮጵያ ምጣኔ ሐብት ዘንድሮ በ8.4 በመቶ ያድጋል በማለት የሐገሪቱ መንግሥት የነደፈዉ ዕቅድ ገቢር እንደሚሆን ጠቋሚ ምልክቶች መኖራቸዉን አስታወቀ።አንድ የምጣኔ ሐብት ባለሙያ ግን የመንግሥትን ዕቅድና ግምት አልተቀበለቱም።ባለሙያዉ እንደሚሉት ሠላም ሳይሰፍን የምጣኔ ሐብት ዕድገት አይኖርም።"የኢኮኖሚ ዕድገት ሁል ጊዜ ጥሩ እና የተስማማ ፖለቲካ ይፈልጋል" ያሉት ባለሙያው የምጣኔ ሐብት ዕድገት አልሚዎችን የሚስብ ኹኔታ ይፈልጋል በማለትም ይከራከራሉ

መንግሥት በዓመቱ የ 8.4 የኢኮኖሚ ዕድገት እቅድ ይዟል

የኢትዮጵያ የፕላን እና ልማት ሚኒስትር ፍፁም አሰፋ ሰሞኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበትት ለመንግሥት የካቢኔ አባላት የሀገሪቱን የዘጠኝ ወራት የምጣኔ ሐብት የሥራ አፈፃፀም ሲያቀርቡ መንግሥት የያዘውን የ8.4 በመቶ የኡኮኖሚ ዕድገት ውጥን ሊያሳካ የሚችልበት ያሏቸው አመላካቾችን ዘርዝረዋል። ከሀገሪቱ ጠቅላላ ምርት አንፃር "ቁጠባ እና ኢንቨስትመንት ማደጋቸውን፣ የሀገር ውስጥ ገቢ መጨመሩን፣ የ3.5 ቢሊዮን ዶላር የዕዳ ሽግሽግ መደረጉ ለዕዳ መከፈል የነበረበት ሀብት ለልማት ሥራዎች ውሎ እገዛ ማድረጉን፣ የውጭ ምንዛሪ ክምችት ማደጉን" በዐወንታ ጠቅሰዋል።

ይህ የሚሳካ አይደለም - የምጣኔ ሐብት ባለሙያ

የመንግሥትን እቅድ በተመለከተበአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የምጣኔ ሐብት መምህር ለሆኑት ዶክተር አጥላው ዓለሙ ጥያቄ አንስተናል። ባለሙያው ለውጥ እንዲመጣ የዕድገት ወሳኝ የሆኑ ጉዳዮች - የካፒታል፣ የሰው ሀብት እና የቴክኖሎጂ እድገት ጨምሯል ወይ? ሲሉ መልሰው ይጠይቃሉ። የፖለቲካ፣ የባህል፣ የሰላም፣ የሕግ፣ ደንብ እና የአሠራር ኹኔታዎች ለሥራ አመቺ ኹኔታ ሲፈጥሩ የኢኮኖሚ ዕድገት ይኖራል ያሉት ባለሙያው ይህ ካልሆነ ግን "በምኞት ዕድገት የለም" ሲሉ መልሰዋል።

 

ከጥቂት ሳምንታት በፊት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማብራሩያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ግን የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ተጨባጭ ኹኔታ "ጤነኛ" ብለውት ነበር።የምጣኔ ሐብት ባለሙያ እና መምህሩ ዶክተር አጥላው ዓለሙ ግን የኢኮኖሚ ዕድገት "ጥሩ እና የተስማማ ፖለቲካ ይፈልጋል" ባይ ናቸው።

የኢትዮጵዮጵያ ምጣኔ ሐብት ዘንድሮ በ8.4 ከመቶ ዕድገት እንደሚያሳይ የኢትዮጵያ መንግስት አስታዉቀ።አንድ የምጣኔ ሐብት አዋቂ ግን «በምኞች ዕድገት የለም» ይላሉ።ምስል፦ DW/M. Haileselassie

 

የፕላንና ልማት ሚኒስትሯ ፍፁም አሰፋ ባለፉት ስምንት ወራት 2.5 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት መሳብ መቻሉን ተናግረዋል። የምጣኔ ሐብት ባለሙያ እና መምህሩ ዶክተር አጥላው ዓለሙ እንደሚሉት ግን ዕድገትን በተመለከተ የሚቀርቡ የተለጠጡ ቁጥሮች የተለመዱ ናቸው።የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በጦርነት፣ በግጭት፣ ለከተማ ልማት በሚል በቤቶች ማፍረስ፣ መፈናቀል፣ የፀጥታ መናጋት፣ እገታን በመሳሰሉ ችግሮች በተከሰተ የሥራ መቀዛቀዝ እየተፈተነ መሆኑ ተደጋግሞ ተነግሯል።

ሰለሞን ሙጬ

ነጋሽ መሐመድ

ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር

 

 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW