1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ መግለጫ

ረቡዕ፣ ታኅሣሥ 17 2005

አብዛኛዎቹ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በምርጫው ለመሳተፍ ብዙ ቅድመ ሁኔታዎችን ቢያስቀምጡም የራዕይ ፓርቲ ግን በምርጫው ለመሳተፍ መወሰኑን አስታውቀዋል ። መሪዎቹ በሰጡት መግለጫ የኢትዮጵያ መንግሥት በቅርቡ ሁለት ተጨማሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስሮችን መሾሙን ህገ መንግሥቱን የጣሰ በማለት ተቃውመዋል

ምስል DW

የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ የተባለው ተቃዋሚ ፓርቲ በመጪው ሚያዚያ በሚካሄደው የአዲስ አበባና የአካባቢ ምርጫ እንደሚሳተፍ አስታወቀ ። የፓርቲው መሪዎች ዛሬ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት አብዛኛዎቹ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በምርጫው ለመሳተፍ ብዙ ቅድመ ሁኔታዎችን ቢያስቀምጡም የራዕይ ፓርቲ ግን በምርጫው ለመሳተፍ መወሰኑን አስታውቀዋል ። መሪዎቹ በሰጡት መግለጫ የኢትዮጵያ መንግሥት በቅርቡ ሁለት ተጨማሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስሮችን መሾሙን ህገ መንግሥቱን የጣሰ በማለት ሲቃወሙት በየአካባቢው መስተዳደር የተለያዩ ምክንያቶች በመስጠት ቤቶች መፍረሳቸውን የዜግነትን መብት መጣስ ነው በማለት አውግዘውታል ።

ዮሐንስ ገብረ እግዚዘብሔር

ሒሩት መለሰ

ነጋሽ መሐመድ 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW