1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የዶክተር አዲሱ መግለጫ

ረቡዕ፣ ግንቦት 8 2010

ተጠሪነቱ ለኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሆነው የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ከዚህ ቀደም ባቀረባቸው ዘገባዎች በተለያዩ አካባቢዎች በተከሰቱ ግጭቶች ያልተመጣጠነ ኃይል በመጠቀም የመንግሥት አካላትን ተጠያቂ ማድረጉን አስታውቋል።

Äthiopische Menschenrechtskommission
ምስል DW/G. T. Hailegiorgis

የኮሚሺነር አዲሱ መግለጫ

This browser does not support the audio element.

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በሶማሌ እና በኦሮምያ ክልል በደረሰ ግጭት የዜጎች ህገ መንግሥታዊ መብቶች መጣሳቸውን  ለኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከ 3 ወራት በፊት በላከው ዘገባ ማሳወቁን ገለፀ። የከሚሽኑ ሃላፊ ዶክተር አዲሱ ገብረ እግዚአብሔር በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ መሥሪያ ቤታቸው ከዚህ ቀደም ባቀረባቸው ዘገባዎችም በተለያዩ አካባቢዎች በተከሰቱ ግጭቶች ያልተመጣጠነ ኃይል በመጠቀም የመንግሥት አካላትን ተጠያቂ ማድረጉን አስታውሰዋል። ኮሚሽነሩ በኢትዮጵያ በየአካባቢው ስለሚፈናቀሉ ሰዎች እና ስለሚፈፀሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች የሰጡትን ጋዜጣዊ መግለጫ የተከታተለው የአዲስ አበባው ወኪላችን ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ተከታዩን ዘገባ ልኮልናል።

ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW