የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ማሻሻያና የፈጠረዉ መጨናነቅ
ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 6 2012ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአገልግሎት ማሻሻያ ለማድረግ ባለፈው ሳምንት ከሀሙስ እስከ እሁድ እለት ድረስ መደበኛ የባንክ አገልግሎቱን በማቋረጡ በዚህኛው የሳምንቱ መጀመርያ ቀናት ላይ ከፍተኛ መጨናነቅና ወረፋ አስከትሏል።ባንኩ ችግሩ እንዲስተካከል ባለሙያዎቻችን ከፍተኛ ስራ ሰርተዋል ቢልም ደንበኞች ዛሬም ድረስ አገልግሎቱን ለማግኘት ረጃጅም ሰልፍ ይዘው ተስተውለዋል። እንዲህ ያለው አሰራር ለኮሮና ወረርሽኝ ሊያጋልጥ ስለሚችል ባንኩ መላ እንዲፈልግም ደንበኞች ጠይቀዋል።
ሰለሞን ሙጬ
ታምራት ዲንሳ
ሂሩት መለሰ