የኢትዮጵያ አዉሮፕላን መረጃ1 የካቲት 2002ሰኞ፣ የካቲት 1 2002የዛሬ ሁለት ሳምንት ከሊባኖስ ቤይሩት ወደአዲስ አበባ በረራ ወጥኖ ከመነሻዉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዉሮፕላን በአየር ላይ ተበታትኖ ከሜዲትራኒያን ባህር መዉደቁ ይታወሳል።ማገናኛዉን ኮፒ አድርግየቤይሩት አዉሮፕላን ማረፊያምስል picture-alliance/ dpaማስታወቂያ የበረራ ቁጥር 409 አዉሮፕላን ለገጠመዉ አደጋ ያበቃዉ ምክንያት እስካሁን አልታወቀም። ያን ለማወቅ ከሚረዱ የበረራ መረጃ መመዝገቢያ ቁሳቁስ መካከል ሁለቱ መገኘቱን የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ቴክኒክ አገልግሎት መምሪያ ሃለፊ ና የዚህ አደጋ መረጃ ተከታታይ ግብረሃይል የበላይ ካፒቴን ደርስታ ዘርዑ ዛሬ ለዶቼ ቬለ አረጋግጠዋል። ሸዋዬ ለገሠ ተክሌ የኋላ