1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢንተርኔት አገልግሎት መቆራረጥ መንስኤ

ረቡዕ፣ ሰኔ 26 2011

ኢትዮ ቴሌኮም በሃገሪቱ ተዘግቶ የሰነበተው የ ፊክስድ ብሮድ ባንድ እና የሞባይል ኢንተርኔት የተቋረጠው ሊያስከትል የሚችለውን ጉዳት ግምት ውስጥ በማስገባት ተወስኖ  እንደሆነ  ለዶይቼ ቬለ DW ገለፀተ።  በተገልጋዮች በኩል  ለተፈጠረው  መጉላላት እና  ለደረሰው የኢኮኖሚ  ኪሳራም  ይቅርታ  ጠየቀ።

Äthiopien Cherer Aklilu
ምስል Solomon Muchie

ኢትዮ ቴሌኮም ይቅርታ ጠይቋል

This browser does not support the audio element.

 የፊክስድ ብሮድ ናንድ አገልግሎቱ  ከሰኔ 18  ጀምሮ  መለቀቁን  የገለጸው  ኩባንያው  የስልክ  ኢንተርኔት  በአሁኑ  ጊዜ በመላ  ሀገሪቱ  ተለቋል  ብሏል። ዶይቼ ቬለ ባደረገው ማጣራት ግን አሁንም  የስልክ ኢንተርኔት  የማይሠራባቸው የሀገሪቱ  ክፍሎች  መኖራቸውን  ለማወቅ  ተችሏል። ኩባንያው በበኩሉ እንዲህ  ያለው  ችግር  እንዳይደጋገም  ምን ይበጃል  የሚለውን  በመለየት የመፍትሄ  እያፈላለገ መሆኑን ይናገራል። ያነጋገርናቸው ግለሰብ እንዳሉት ከሆነ ግን ችግሩ መነሻው መንግስት ነጻ የሆኑና ሃቀኛ መገናኛ ብዙሃን መፍጠር ባለመቻሉ ሰው ትኩረቱን ማህበራዊ መገናኛዎች ላይ በማድረጉ የመጣ በመሆኑ ሊያስብበት ይገባል ብለዋል። የተጠቃሚዎችን አስተያየት በማካተት ከአዲስ አበባ ሰሎሞን ሙጬ ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።

ሰሎሞን ሙጬ

ሸዋዬ ለገሰ

ኂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW