የኢንተርኔት አገልግሎት መቆራረጥ መንስኤ
ረቡዕ፣ ሰኔ 26 2011ማስታወቂያ
የፊክስድ ብሮድ ናንድ አገልግሎቱ ከሰኔ 18 ጀምሮ መለቀቁን የገለጸው ኩባንያው የስልክ ኢንተርኔት በአሁኑ ጊዜ በመላ ሀገሪቱ ተለቋል ብሏል። ዶይቼ ቬለ ባደረገው ማጣራት ግን አሁንም የስልክ ኢንተርኔት የማይሠራባቸው የሀገሪቱ ክፍሎች መኖራቸውን ለማወቅ ተችሏል። ኩባንያው በበኩሉ እንዲህ ያለው ችግር እንዳይደጋገም ምን ይበጃል የሚለውን በመለየት የመፍትሄ እያፈላለገ መሆኑን ይናገራል። ያነጋገርናቸው ግለሰብ እንዳሉት ከሆነ ግን ችግሩ መነሻው መንግስት ነጻ የሆኑና ሃቀኛ መገናኛ ብዙሃን መፍጠር ባለመቻሉ ሰው ትኩረቱን ማህበራዊ መገናኛዎች ላይ በማድረጉ የመጣ በመሆኑ ሊያስብበት ይገባል ብለዋል። የተጠቃሚዎችን አስተያየት በማካተት ከአዲስ አበባ ሰሎሞን ሙጬ ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።
ሰሎሞን ሙጬ
ሸዋዬ ለገሰ
ኂሩት መለሰ