የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በባለሙያዎች ሲገመገም
ረቡዕ፣ የካቲት 27 2011ማስታወቂያ
ፕሮፈሰር ጌታቸው በጋሻው በዩናይትድ ስቴትስ ቺካጎ ክፍለ ግዛት ሀርፐር ኮሌጅ የምጣኔ ሀብት መምህር ናቸው። በዚያው በአሜሪካ ቨርጂኒያ በሚገኘው ኮሌጅ ኦፍ ዊሊያም ሜሪ መምህር የሆኑት ዶ/ር ብርሃኑ አበጋዝም በተመሳሳይ የትምህርት ዘርፍ ያስተምራሉ። በአንድ ሀገር እንዴት ኢንቨስትመንት ሊመጣ ይችላል? የምጣኔ ሀብት ለማምጣት ዋናው ትኩረት ምን ይሆን? ኢትዮጵያስ በአሁኑ ወቅት ምን ማድረግ አለባት? ለሚሉት ጥያቄዎች ባለሙያዎቹ ማብራሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ፕሮፌሰር ጌታቸው “የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በማንኛውም የኢኮኖሚ ስርዓት ለመገለጽ የማይችል፣ በየትኛውም የኢኮኖሚ ሞዴል ለመተንተን የማይቻል፣ አስቸጋሪ የሆነ እና በዘፈቀደ የሚካሄድ ነው ሲሉ ይተቻሉ”። ዶ/ር ብርሃኑ በበኩላቸው ያለፉት ዓመታት የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ “መንግስት መር” ነው ይላሉ። “በፓርቲ የተያዘ መንግስት የሚመራው የኢኮኖሚ እድገት ነው” ሲሉ ያክላሉ።
የዋሽንግተኑ ዘጋቢያችን መክብብ ሸዋ ያሰናውን ሙሉ ጥንቅር ለማድመጥ የድምጽ ማዕቀፉን ይጫኑ።
መክብብ ሸዋ
ተስፋለም ወልደየስ