የኢትዮጵያ እና ኬንያ የንግድ ግንኙነት
ዓርብ፣ የካቲት 22 2011ማስታወቂያ
ጉባኤው የሁለቱን ሃገራት የንግድ እና የመዋዕለ ንዋይ ፍሰት ትስስር እንደሚያጠናክር ተገምቷል። በተያያዘ ዜናም የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ እና የኬንያው ፕሬዝደንት ዑሁሩ ኬንያታ ዛሬ የሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክን እንደጎበኙ የሀዋሳው ዘጋቢያችን ሸዋንግዛው ወጋየሁ የላከልን ዘገባ ያስረዳል።
በጉብኝቱ ወቅትም የሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ ሥራ አስኪያጅ አቶ ፍፁም ከተማ የፕሬዝዳንቱ ጉብኝት የሁለቱን ሃገራት ምጣኔ ሀብት በንግድና በመዋዕለንዋ ፍሰት ለማስተሳሰር የተጀመረውን ጥረት የማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽዎ እንዳለው ማመልከታቸውን ሸዋንግዛው በላከው ዘገባ አመልክቷል።
ሸዋንግዛው ወጋየሁ
ነጃት ኢብራሒም
ማንተጋፍቶት ስለሺ