1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ እና ኬንያ የንግድ ግንኙነት

ዓርብ፣ የካቲት 22 2011

በኢትዮጲያ ሁለት ቀናት የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ ጠዋት አዲስ አበባ የገቡት ፕሬዝዳንት ኡሁሩ በአሁኑ ሰዓት አዚህ ሀዋሳ በመገኘት የሀዋሳን እንዱስትሪል ፓርክ በመጎብኘት ላይ ይገኛሉ፡፡ አዲስ አበባ ላይ ደግሞ ከመቶ በላይ የኬንያ እና የኢትዮጵያ የንግድ ማኅበረሰብ የተገኙበት የንግድ ጉባኤ እየተካሄደ ነው።

Stadtansicht von Addis Abeba Hauptstadt von Aethiopien
ምስል Imago/photothek

መሪዎቹ የሀዋሳን ኢንዱስትሪ ፓርክ ጎብኝተዋል

This browser does not support the audio element.

 ጉባኤው የሁለቱን ሃገራት የንግድ እና የመዋዕለ ንዋይ ፍሰት ትስስር እንደሚያጠናክር ተገምቷል። በተያያዘ ዜናም የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ እና የኬንያው ፕሬዝደንት ዑሁሩ ኬንያታ ዛሬ የሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክን እንደጎበኙ የሀዋሳው ዘጋቢያችን ሸዋንግዛው ወጋየሁ የላከልን ዘገባ ያስረዳል። 

በጉብኝቱ ወቅትም  የሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ ሥራ አስኪያጅ አቶ ፍፁም ከተማ የፕሬዝዳንቱ ጉብኝት የሁለቱን ሃገራት ምጣኔ ሀብት በንግድና በመዋዕለንዋ ፍሰት ለማስተሳሰር የተጀመረውን ጥረት የማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽዎ እንዳለው ማመልከታቸውን ሸዋንግዛው በላከው ዘገባ አመልክቷል።

ሸዋንግዛው ወጋየሁ
ነጃት ኢብራሒም
ማንተጋፍቶት ስለሺ
 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW