የእርቅ ዳስ
ማክሰኞ፣ ታኅሣሥ 14 2012![Äthiopien Eritrea l Celebrity Events - Friedensmission](https://static.dw.com/image/51788554_800.webp)
ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ እና የኤርትራን ግንኙነት ይበልጥ ለማሻሻል እና የሁለቱን ህዝቦች ተጠቃሚነት ለማሳደግ በህወኃት እና በኤርትራው ገዥ ድርጅት ህዝባዊ ግንባር ንዲሞክራሲን ፍትህን ( ህግዴፍ ) መካከል እርቅ ያስፈልጋል ተባለ።ላለፉት 4 አመታት በሁለቱ ሃገራት መካከል እርቅ እንዲወርድ ጥረት ማድረጉን የሚገልጸው ሰለብሪቲ ኢቨንትስ የተባለ ድርጅት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አደረግኩት ባለው ጥናት ድንበር አካባቢ ያለው ህዝብ የሁለቱ ድርጅቶች አመራሮች እርቅ ባለማውረዳቸው ለተለያዩ ችግሮች ተዳርጓል።ችግሮቹን ለመፍታትም ከ 20 በላይ አባላትን የያዘ "የእርቅ ዳስ" በሚል መርህ እርቅ የሚያፈላልግ ልዑክ ይዞ ወደ አስመራ በቅርቡ እንደሚጓዝ ይፋ አድርጓል።ሰሎሞን ሙጬ ከአዲስ አበባ ዝርዝሩን አዘጋጅቷል።
ሰሎሞን ሙጬ
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ