1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ግንኙነት ቀጣይ ግንኙነት እንዴት?

ሰኞ፣ ነሐሴ 14 2010

የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ቀጣይ ግንኙነት አንድ ህዝብ ሁለት ሀገር በሚል መርኅ ላይ የተመሰረተ ሊሆን እንደሚገባ ዶክተር ተከስተ ነጋሽ ያምናሉ። ይኸ ግን ምን ማለት ነው?

Äthiopien Eritrea eröffnet Botschaft beim einstigen Kriegsgegner
ምስል Reuters/T. Negeri

MMT/Dr. Tekeste Negash on durable peace between Ethiopia and Er - MP3-Stereo

This browser does not support the audio element.

ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ለዓመታት ጥርጣሬ እና ሥጋት የተጫነው ግንኙነታቸውን ለማደስ በቆረጡ በጥቂት ሳምንታት ልዩነት በአፍሪቃ ቀንድ ቀጣና የነበረው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በፍጥነት ይቀየር ይዟል። የሶማሊያ እና የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንቶች ወደ አስመራ ጎራ እያሉ በሁለትዮሽ እና የቀጣናው ፖለቲካ ላይ ከፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር እየተመካከሩ ነው። መንገዱን የከፈተው ከረዥም አመታት ማመንታት በኋላ ኢሕአዴግ የአልጀርስ ውሳኔን ለመቀበል ያሳለፈው ውሳኔ ቢሆንም የተባበሩት አረብ ኢሚሬቶችን የመሳሰሉ አገራት ላቅ ያለ ሚና ተጫውተዋል። እስካሁን በፖለቲከኞች የሚቀነቀነው የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ወዳጅነት እንዴት ይዘልቃል?  የኢትዮጵያ እና የኤርራን ግንኙነት ቀረብ ብለው ያጠኑት ዶክተር ተከስተ ነጋሽን የብራስልሱ ወኪላችን ገበያው ንጉሴ አነጋግሯቸዋል። 

ገበያው ንጉሤ

እሸቴ በቀለ

ነጋሽ መሀመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW