1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክርስትያን ጥሪ 

ዓርብ፣ ጥቅምት 14 2012

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ባስተላለፈው የሰላም ጥሪ በሃገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች በልዩ ልዩ ምክንያቶች መጠነ ሰፊ ግጭቶች በመከሰታቸው የሰው ህይወት መጥፋቱን በርካታ ንብረት መውደሙን አስታውሷል።ችግሩ እጅግ አሳሳቢ መሆኑን ገልጾ ሁሉም ኢትዮጵያዊያ በአንድነትና በህብረት ከባድ ጉዳት የሚያስከትለው ያለውን ይህን ችግሩን እንዲያስወግድ ጠይቋል።

Äthiopien | Orthodox Church press briefing
ምስል DW/S. Muchie

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጸሎትና ምህላ አወጀች

This browser does not support the audio element.

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን ከዛሬ ጥቅምት 13፣ 2012 ዓ.ም ጀምሮ ለ ሶስት ቀናት  የሚዘልቅ የጸሎትና ምህላ መንፈሳዊ አዋጅ አወጀች።ቤተ ክርስትያኗ ያለ ሃገር ሰላምና አንድነት እንዲሁም ፍቅርና እድገት መኖር ስለማይችል መላው ህዝብ እንደየእምነቱና ሃይማኖቱ ስርአት ከዛሬ ጀምሮ ለ ሶስት ቀናት ያህል በጾም ፣በጸሎትና በሃዘን ስለ ሃገር ሰላም በአንድነት ጥሪውን ለፈጣሪውና ለአምላኩ ያደርስ ዘንድ ጥሪ አቅርባለች ። መንፈሳዊ አዋጁንም አውጃለች። የቤተክርስትያኗ ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ባስተላለፈው የሰላም ጥሪ በሃገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች በልዩ ልዩ ምክንያቶች ብሄርና ሀይማኖትን እንዲሁም ቋንቋን መሰረት ያደረገ መጠነ ሰፊ ግጭቶች በመከሰታቸው የሰው ህይወት መጥፋቱን በርካታ ንብረት መውደሙን አስታውሷል።ችግሩ እጅግ አሳሳቢ ከመሆኑም በላይ ጊዜ የማይሰጥ መሆኑን ገልጾ ሁሉም ኢትዮጵያዊያ በአንድነትና በህብረት ከባድ ጉዳት የሚያስከትለው ያለውን ይህን ችግሩን እንዲያስወግድ ጠይቋል።መግለጫውን የተከታተለው የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ዝርዝሩን አዘጋጅቷል።


ሰሎሞን ሙጬ 


ኂሩት መለሰ
ተስፋለም ወልደየስ 
 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW