የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሲኖዶስ ዉግዘትና ዉሳኔ
ረቡዕ፣ የካቲት 11 2012ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስትያን ቅዱስ ሲኖዶስ ባለፈ ጥር ማብቂያ በአዲስ አበባ ዉስጥ ሁለት ምዕመናን መገደላቸዉንና ሌሎች መጎዳታቸዉን አወገዘ።በሌላ በኩል ከቤተ ክርስትያኒቱ ህግና ደንብ ውጪ፣ የኦሮሚያ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት እናቋቁማለን በማለት የሚንቀሳቀሱ ባላቸው ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኮንን ፣ አባ ገብረ ማርያም ነጋሳ፣ መምህር ኃይለሚካኤል ታደሰ እና ቄስ በዳሳ ቶላ ላይ ከዛሬ ጀምሮ ከቤተ ክርስትያን የተሰጣቸው ክህነት መያዙንና በቤተ ክርስትያኒቱ ስም ምንም አይነት እንቅስቃሴ እንዳያደርጉ አግዷል።
ሰለሞን ሙጬ
ነጋሽ መሐመድ
ኂሩት መለሰ