1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የተመድ አስተያየት

ሐሙስ፣ ጥቅምት 24 2009

በተመድ የፖለቲካ ጉዳዮች ተጠሪ ሆዜ ሉስየስ ለዶቼቬለ እንደተናገሩት ድርጅታቸው ኢትዮጵያ ከሶማልያ ወታደሮችዋን እንደምታስወጣ አስቀድሞ አልተነገረውም ።

Somalia Islamisten fliehen aus somalischer Hafenstadt Kismayo
ምስል፦ picture-alliance/ dpa

Beri Wash.(UN rxn on Ethiopian troops withdrawal from Somalia) - MP3-Stereo

This browser does not support the audio element.

ኢትዮጵያ ወታደሮቿን ከሶማሊያ ስታስወጣ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እንዳላሳወቀች ተነገረ ። በተመድ የፖለቲካ ጉዳዮች ተጠሪ ሆዜ ሉስየስ ለዶቼቬለ እንደተናገሩት ድርጅታቸው ኢትዮጵያ ከሶማልያ ወታደሮችዋን እንደምታስወጣ አስቀድሞ አልተነገረውም ። የቀድሞ የኢትዮጵያ መንግሥት ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ ኢትዮጵያ  በራስዋ ወጭ ሶማሊያ ያዘመተቻቸውን ወታደሮቿን በገንዘብ ችግር ምክንያት እንዳስወጣች ባለፈው ሳምንት ተናግረው ነበር ። የመንግሥታቱ ድርጅት ባለሥልጣን ሉስየስ እንዳሉት ድርጅታቸው  የኢትዮጵያ ወታደሮች በመውጣታቸው የተፈጠረውን ክፍተት ለመሙላት ሌሎች አባላትን እየጠየቀ መሆኑን አስታውቀዋል ።

መክብብ ሸዋ

ኂሩት መለሰ

አዜብ ታደሰ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW