የህግ ማሻሻያ
ሰኞ፣ ሰኔ 25 2010![Berhanu Tsegaye](https://static.dw.com/image/44491013_800.webp)
ማስታወቂያ
በቅርቡ የተቋቋመው የህግ እና ፍትህ ጉዳዮች አማካሪ ጉባኤ የኢትዮጵያን የፍትህ ስርዓት ለማሻሻል የሚያስችሉ ሀሳቦችን ለመንግሥት እንደሚያቀርብ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ አቶ ብርሃኑ ፀጋዬ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተናግረዋል። ጉባኤው መስተካከል ያለባቸው እንዲስተካከሉ፣ አዳዲስ ሃሳቦችም እንዲካተቱ እና መለወጥ የሌለባቸውም እንዲቀጥሉ እንደሚያደርግ የጉባኤው አባል የሆኑት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የህግ መምህር ፕሮፌሰር ጥላሁን ተሾመ ለዶቼቬለ ተናግረዋል። ህጎችን ስራ በማዋል ረገድ የተቋማዊ መዋቅሮች ሚና እና የዳኝነት ነጻነት አማካሪው ጉባኤ ከሚፈትሻቸው ጉዳዮች ውስጥ እንደሚገኙበት ፕሮፌሰር ጥላሁን አስረድተዋል።
ጌታቸው ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ