የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የሥልጣን ውዝግብ
ሰኞ፣ ታኅሣሥ 16 2010
ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) የአመራርነት ሥልጣኑ ይገባኛል በሚል የአባላት ክርክር ይታመስ ይዟል። አቶ አዳነ ታደሰ በአንድ በኩል እንዲሁም እስካሁን በፕሬዝዳንትነት የሚታወቁት ዶ/ር ጫኔ ከበደ በተቃራኒው ሆነው የይገባኛል ውዝግቡን ይመሩታል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በበኩሉ አቶ አዳነ ታደሰ የተመረጡት ምልዓተ-ጉባኤ ሳይሟላ በመሆኑ የድርጅቱን ማሕተም ሊጠቀሙ አይገባም ብሏል። የቀድሞው የፓርቲው ፕሬዝዳንት አቶ ልደቱ አያሌው በወገናቸው የምርጫ ቦርድን ቅሬታ አዳምጠን በዛሬው ዕለት በሕገ-ደምቡ መሰረት አቶ አዳነ ታደሰ ፕሬዝዳንት አድርገን መርጠናል እያሉ ነው።
ጌታቸው ተድላ ወልደጊዮርጊስ
ነጋሽ መሐመድ