1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ ጦር ተመልሶ ሶማሊያ ገባ ተባለ

ማክሰኞ፣ ጥር 26 2001

በፌርፌር አካባቢ የሚገኙ አንዳንድ ነዋሪዎች እንደገለፁት፤ የኢትዮጵያ ወታደሮች በአካባቢው የፍተሻ ጣቢያ አቓቁመው ተሽከርካሪዎችን እየተቆጣጠሩ ነው። በኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ የምትገኘው የበለድወይኔ ነዋሪዎች በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያ ወታደሮች ድንበር ዘልቀው ሃያ ኪሎ ሜትር ገብተዋል ሲሉ ለሮይተር እማኝነታቸውን ገልፀዋል።

የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሼክ ሸሪፍ ሼክ አህመድ
የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሼክ ሸሪፍ ሼክ አህመድምስል AP

ኢትዮጵያ ጦሯን ሙሉ ለሙሉ ከሶማሊያ ማስወጣቷን በገለፀች በጥቂት ቀናት ውስጥ ተመልሳ ወደ ሶማሊያ መግባቷን አንዳንድ የዜና ምንጮች እማኞችን በመጥቀስ ዛሬ ዘገቡ። የኢትዮጵያ የመገናኛ ወይንም የኮሚኒኬሽን ሚንስትር አቶ በረከት ስምኦን “ይህ መሰረተ ቢስ መረጃ ነው” ሲሉ ዛሬ ለዶቸቬለ በሰጡት ቃለመጠይቅ አስተባብለዋል። ኢትዮጵያ ወደ ሶማሊያ ተመልሳ ከገባች ሁኔታው አሳሳቢ እንደሚሆን በለንደን የቻተም ሀውስ የአፍሪቃ ቀንድ ጉዳይ ተንታኟ ሚስ ሳሊ ሂሊ ገልፀዋል።

Mantegaftot Silshi

Negash Mohammed

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW