1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ ፍርድ ቤቶች ውሎ 

ረቡዕ፣ ግንቦት 2 2009

ከ50 በላይ ሰዎች በሞቱበት የኢሬቻ ተቃውሞ እና አደጋ የኢትዮጵያ መንግሥት ክስ የመሰረተባቸው 9 ተጠርጣሪዎች ጉዳይ በፍርድ ቤት መታየት ጀመረ።

Äthiopien Journalisten Martin Schibbye und Johan Persson
ምስል AP

Ber. A.A. (Court hearing_anti terrorists act in Erecha ceremony ) - MP3-Stereo

This browser does not support the audio element.

የኢትዮጵያ ፍርድ ቤቶች ዛሬ ሥራ በዝቶባቸው ውሏል። ከ50 በላይ ሰዎች በሞቱበት የኢሬቻ ተቃውሞ እና አደጋ የኢትዮጵያ መንግሥት ክስ የመሰረተባቸው 9 ተጠርጣሪዎች ጉዳይ በፍርድ ቤት መታየት ጀመረ። ከሰባት ወራት እስር በኋላ ዛሬ ፍርድ ቤት የቀረቡት ግለሰቦች የእምነት ክሕደት ቃላቸውን ዛሬ ሰጥተዋል። በእነ ቀመር ሐጂ መዝገብ የተካተቱት 9 ሰዎች የሽብር ክስ እንደተመሰረተባቸው ጠበቃቸው ተናግረዋል። የቀድሞው የሰማያዊ ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ በአቶ ዮናታን ተስፋዬ ላይ የመጨረሻ ፍርድ ይሰጣል ተብሎ የተጠበቀው ችሎት ብያኔ አልደረሰልኝም በማለት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። የአቶ ዮናታን ተስፋዬ የክስ ሒደት 1 አመት ከ5 ወር አስቆጥሯል። 
ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር
እሸቴ በቀለ
አዜብ ታደሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW