1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮ ምህዳር ዋና አዘጋጅ መፈታት

ሰኞ፣ ሰኔ 26 2009

የሳምንታዊው ኢትዮ ምህዳር ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ጌታቸው ወርቁ ከእስር ተፈታ። ጋዜጠኛ ጌታቸው የታሰረው በአዲስ አበባ በኦርቶዶክስ ቤ/ክርስትያን መንበረ ፓትርያርክ ቅድስት ማርያም ገዳም ውስጥ አለ ስለተባለ ችግር በማስረጃ አስደግፎ ከአንድ ዓመት ከአምስት ወር በፊት ዘገባ በማቅረቡ ባለፈው ህዳር በስም ማጥፋት ወንጀል ክስ ከተመሰረተበት በኋላ ነው።

Waage der Göttin Justitia
ምስል dpa

Ber. AA(Ethio Mehdar Journalist Getachew Worku freigelassen) - MP3-Stereo

This browser does not support the audio element.

የአንድ ዓመት እስራት እና የገንዘብ ቅጣት ክፍያ ተፈርዶበት የነበረው እና ጋዜጣውም የተዘጋበት  ጋዜጠኛ ጌታቸው ወርቁ፣ የአዲስ አበባ ዘጋቢያችን ዮሐንስ ገብረእግዚአብሄር እንደገለጸልን፣ ትናንት በአመክሮ ተፈቷል፣ የመዘጋት እጣ ያጋጠመውን «ኢትዮ ምህዳር»ን መልሶ የመጀመር ፍላጎትም አለው። የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ጋዜጠኛ ጌታቸው ወርቁን አነጋግሮታል።  

ዮሐንስ ገብረእግዚአብሄር

አርያም ተክሌ

ሂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW