1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የኢትዮ-ሱዳን የድንበር ዉዝግብ

ማክሰኞ፣ ታኅሣሥ 20 2013

የሱዳን ጦር፣ ኢትዮጵያዉያን ገበሬዎች ተቆጣጥረዉት ነበር ያለዉን የሱዳን ግዛት መልሶ መቆጣጠሩን ባለፈዉ ሳምንት ማብቂያ አስታዉቋል።የኢትዮጵያ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ዛሬ በሰጠዉ መግለጫ እንዳስታወቀዉ ግን የሱዳን ጦር የያዘዉ የኢትዮጵያን ግዛት ነዉ

Äthiopien Dina Mufti

የኢትዮጵያና የሱዳን የአዋሳኝ ድንበር ግዛት ይገባኛል ዉዝግብ

This browser does not support the audio element.

                            

የኢትዮጵያና የሱዳን መንግስታት በድንበር ግዛት ይገባኛል ሠበብ የገጠሙት ዉዝግብ እየተካረረ ነዉ።ሁለቱ ሐገራት በዉል ባልተከለለ የድንበር ግዛት ይገባኛል ሰበብ ሲወዛገቡ ያሁኑ የመጀመሪያቸዉ አይደለም።ይሁንና ዉዝግቡ የሰሞኑን ያክል ጦር ወዳማዘዘ እሰጥ አገባ ተካርሮ አያዉቅም።የሱዳን ጦር፣ ኢትዮጵያዉያን ገበሬዎች ተቆጣጥረዉት ነበር ያለዉን የሱዳን ግዛት መልሶ መቆጣጠሩን ባለፈዉ ሳምንት ማብቂያ አስታዉቋል።የኢትዮጵያ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ዛሬ በሰጠዉ መግለጫ እንዳስታወቀዉ ግን የሱዳን ጦር የያዘዉ የኢትዮጵያን ግዛት ነዉ።የዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ ዲና ሙፍቲ ከሱዳን ጀርባ «ለሱዳንም ለኢትዮጵያም የማይጨነቁ» ያሏቸዉ ግን በስም ያልጠቀሷቸዉ ኃይላት መኖራቸዉን ጠቅሰዋል።

ሠለሞን ሙጬ 

ነጋሽ መሐመድ

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW