የኢትዮ-ኤርትራ ሥምምነት
ዓርብ፣ መስከረም 18 2011![Äthiopien Begeisterter Empfang für Präsident Isaias an Adis Abeba](https://static.dw.com/image/44701050_800.webp)
ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ እና የኤርትራ መሪዎች የተፈራረሙት የሠላም ሥምምነት 20 ዓመት ያስቆጠረዉን የሁለቱን ሐገራት ጦርነት እና ግጭት በማስወገዱ ከሁለቱ ሐገራት ሕዝብ አልፎ ዓለም አቀፍ ድጋፍ እና አድናቆት አትርፏል። ይሁንና አስተያየት ሰጪዎች እንደሚሉት ሁለቱ መሪዎች ባለፈዉ ሐምሌ አስመራ-ኤርትራ፤ ከጥቂት ሳምታት በፊት ደግሞ ጂዳሕ ሳዑዲ አረቢያ የተፈራረሙት ዉል ዝርዝር ይዘቱ ለሕዝብ ይፋ አልተደረገም በማለት ይተቻሉ። የሁለቱ ሐገራት ባለሥልጣናት ግን የሥምምነቱ ይዘት በተደጋጋሚ ጋዜጣዊ መግለጫ መብራራቱ እና በዓምደ መረብ መሰራጨቱን ይናገራሉ።
ዳግማዊ ሲሳይ
ነጋሽ መሐመድ
ሸዋዬ ለገሠ