1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር ስምምነት መፍረስ እና የሰራተኞች እጣ ፈንታ

ቅዳሜ፣ ሚያዝያ 22 2014

የኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር ይተዳደርበት የነበረው የሁለት ሃገራት ሕጋዊ ስምምነት ፈርሶ ተቋሙ በድሬዳዋ አስተዳደር ስር እንዲሆን በሚኒስትሮች ምክር ቤት የተላለፈ ውሳኔ ከሰራተኞቹ ዘንድ በርከት ያሉ ጥያቄዎች አስነስቷል። የድርጅቱ ቦርድ ሰብሳቢ ሆነው የተመደቡት የድሬዳዋ ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ ተቀጣሪዎች ከሥራቸው እንደማይፈናቀሉ ተናግረዋል

Äthiopien Dire Dawa | Sultan Aliye, Kedir Juhar, Dire Dawa City Mayor & Harbi Buh Ethio-Djibouti
ምስል፦ Messay Teklu/DW

የኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር ስምምነት መፍረስ እና የሰራተኞች እጣ ፈንታ

This browser does not support the audio element.

የኢትዮ - ጅቡቲ ምድር ባቡር ድርጅት ይተዳደርበት የነበረው የሁለት ሃገራት ሕጋዊ ስምምነት ፈርሶ በድሬዳዋ አስተዳደር መግባቱን ተከትሎ ሠራተኞች ለአስተዳደሩ የተለያዩ ጥያቄዎችን አንስተዋል። የድርጅቱ ሠራተኞች ሰሞኑን ጥያቄያቸውን ያነሱት የሚንስትሮች ምክር ቤት በድርጅቱ ስር ያሉ ቋሚ ሠራተኞች እና ንብረት በድሬዳዋ አስተዳደር ስር እንዲተዳደር ያሳለፈውን ውሳኔ ተከትሎ ድርጅቱ ከሠራተኞቹ ጋር ባደረገው ውይይት ነው። ሠራተኞች ለዘመናት በበረሀ ንዳድ እና ቃጠሎ ሲንገላቱ የበረሃ አበል ሳይሰጣቸው መቆየታቸውንም በምሬት ተናግረዋል። እጣ ፈንታቸው ምን እንደሆነም ግራ መጋባታቸውን ገልጠዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር፦ «የፈረሰው የኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር የሚለው ስምምነቱ ነው እንጂ ድርጅቱ አልፈረሰም» የሚል ምላሽ ሰጥተዋል። የድሬዳዋው ወኪላችን መሣይ ተክየሰሞኑን ውይይት ተከታትሎት ነበር። 

የኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር ሠራተኞችምስል፦ Messay Teklu/DW

እጅግ ዝቅተኛ በሆነ ወርሀዊ ደሞዝ ከማገልገል ባለፈ ፤ ለአስተዳደሩም ሆነ በአስተዳደሩ ውስጥ ለሚገኙ የፌደራል ተቋማት ሰራተኞች እየተከፈለ የሚገኘው የበረሀ አበል ክፍያ እየተከፈላቸው አለመሆኑም በጥያቄ ቀርቧል።

በተለያዩ ጊዜያት በተለያዩ አደረጃጀቶች ስር እንዲገባ እየተደረገ ህልውናው በመክሰም ጫፍ ላይ በደረሰው የምድር ባቡር ድርጅት ዙርያ በቅርብ እየወጡ ባሉ ውሳኔዎች ሀሳብ ግር መሰኘታቸውን አንስተዋል።

ረዥም ዕድሜ ያስቆጠረው የኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር ድርጅት ምስል፦ Messay Teklu/DW

ውሳኔው የቀደመ እሴታችንን ዛሬም በተሻለ መልኩ እንድንጠቀም ያስቻለ ታሪካዊ ውሳኔ ነው ያሉት የድሬደዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሀር ስለውሳኔው ምላሽ ሰተዋል። 

በድርጅቱ ቦርድ ሰብሳቢነት የተመደቡት የመስተዳድሩ ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ በበኩላቸው ለብዙዎች ስጋት የሆነው የመፈናቀል ሁኔታ አይኖርም ብለዋል።

መስተዳድሩ በኃላፊነት ለተረከባቸው የድርጅቱ ሰራተኞች ከመጪው ግንቦት ወር ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን የ20 በመቶ የበረሀ አበል ጭማሪ እንደሚያደርግ ቃል ገብቷል።

መሳይ ተክሉ

እሸቴ በቀለ
 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW