1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የኢትዮ - ፈረንሳይ ትብብር 125ኛ ዓመት በድሬደዋ

ሐሙስ፣ ጥቅምት 17 2015

የኢትዮ - ፈረንሳይ ትብብር 125ኛ ዓመት ክብረ በዓል አከባበር አካል የሆነ ዝግጅት በድሬደዋ ተካሄደ። ከአንድ ምዕተ አመት በላይ የዘለቀው የሁለቱ ሃገራት ግንኙነት በተለያዩ መስኮች እያደገ መምጣቱም ተገልጿል።

Äthiopien I Ausstellung zum 125. Jahrestag der Zusammenarbeit mit Frankreich in Dire Dawa
ምስል፦ Mesay Tekelu/DW

የኢትዮ - ፈረንሳይ ትብብር

This browser does not support the audio element.

የኢትዮ - ፈረንሳይ ትብብር 125ኛ ዓመት ክብረ በዓል አከባበር አካል የሆነ ዝግጅት በድሬደዋ ተካሄደ። ከአንድ ምዕተ አመት በላይ የዘለቀው የሁለቱ ሃገራት ግንኙነት በተለያዩ መስኮች እያደገ መምጣቱም ተገልጿል። ከምስረታዋ ጀምሮ የተለያዩ ፈረንሳያውያን አሻራ ባረፈባት ድሬደዋ በተካሄደው ዝግጅት በታሪካዊው የኢትዮ - ጅቡቲ የባቡር መስመር ዝርጋታ ባለውለታ የሆነችው ፈረንሳይ ይህንን ሀብት ለቱሪዝም እና ሌሎች አገልግሎቶች ለማዋል በተጀመረው ጥረት የበኩሏን ድጋፍ እንድታደርግ ጥሪ ቀርቧል። በዝግጅቱ በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር ሬኒ ማሪሾ የቱሪዝም ሚንስትሯ ናሲሴ ጫሊ እና የድሬደዋ አስተዳደር ባለሥልጣናት ተገኝተዋል። 
በድሬደዋ በተካሄደው ዝግጅት ላይ የቱሪዝም ሚንስቴር ሚንስትር ናሲሴ ጫሊ የሁለቱን ሃገራት ትብብር 125ኛ ዓመት አስመልክቶ በታሪካዊው የባቡር ድርጅት ውስጥ የተሰናዳው ኤግዚቢሽን በዓሉን ከማብሰር ባለፈ ለቱሪዝም ዘርፉ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት መሆኑን ጠቅሰው ድርጅቱን ለቱሪዝም እና ሌሎች  አገልግሎቶች ለማዋል ለተጀመረው ጥረት በፈረንሳይ በኩል ድጋፍ እንደሚደረግ እምነታቸውን ገልፀዋል። የፈረንሳይ መንግሥት ድሬደዋን ከምስረታዋ ጀምሮ በማዘመን ትልቅ አስተዋፅኦ ስለማበርከታቸው የተለያዩ ማሳያዎችን የጠቀሱት የድሬደዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር ወደፊትም ይኸው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቁመዋል። በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር ሬኒ ማሪሾ በበኩላቸው ሁለቱ ሃገራት በተለያዩ መስኮች በርካታ ትብብር እንዳላቸው ጠቁመዋል። ለሁለቱ ሃገራት ግንኙነት ትልቅ አሻራ በሆነው የቀድሞው የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር የተዘጋጀው ኤግዚቢሽን ትስስሩን ከፍ ለማድረግ ያለውን የጋራ ፍላጎት እንደሚያሳይም ነው የጠቆሙት። «ይህ ኤግዚቢሽን በራሱ ፈረንሳይ እና ኢትዮጵያን አንድ የሚያደርገውን ታሪካዊ ትስስር ብቻ ሳይሆን በቴክኖሎጂ ፈጠራ ልማት እንዲሁም የህዝቡን ደህንነት ለማሻሻል ያለውን ከፍተኛ የጋራ ፍላጎት የሚያሳይ ነው።» የሁለቱን ሃገራት ትብብር 125ኛ ዓመት አስመልክቶ የተለያዩ ዝግጅቶች ተከናውነዋል።

የኢትዮ ጅቡቲ 125 ዓመት አከባበር በድሬደዋምስል፦ Mesay Tekelu/DW
የኢትዮ ጅቡቲ 125 ዓመት አከባበር በድሬደዋምስል፦ Mesay Tekelu/DW

መሳይ ተክሉ

ሸዋዬ ለገሠ

አዜብ ታደሰ
 

ቀጣዩን ክፍል እለፈው የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል እለፈው ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW