የኢንተርኔት አፈና ተባብሷል-ፍሪደም ሃውስ
ሰኞ፣ ጥቅምት 22 2008ማስታወቂያ
የኢንተርኔት መረጃዎችን በይዘታቸው አማካኝነት ማፈን፣ ሰዎችን እርስ በርስ በተለዋወጧቸው መረጃዎች ምክንያት ማሰርና የኢንተርኔት መረጃዎች የሚሰልሉ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም መንግስታት የዜጎቻቸውን የኢንተርኔት ነጻነት እያፈኑ ነው መሆናቸዉን ድርጅቱ ገልጾአል። ግንባር ቀደም የኢንተርኔት አፋኞች ናቸው ካላቸው ሃገራት መካከል ደግሞ ቻይና፣ሶሪያ፣ኢራን፣ኢትዮጵያና ኩባ የገኙበታል። አይስላንድ፣ኢስቶኒያ፣ካናድ፣ጀርመንና አወስትራሊያ የኢንተርኔት ነጻነት ከተረጋገጠባቸው ሀገራት ቀዳሚዎቹ ናቸው። 2.9% ለሆነው ህዝቧ ብቻ የኢንተርኔት አገልግሎት እያቀረበች ያለችው ኢትዮጵያ የማህበራዊ ድረ-ገጾችን ታግዳለች፣የፖለቲካና ማህበራዊ ጉዳዮች ይዘት ያላቸውን መረጃዎች ታፍነለች፣ የኢንተርኔት ጸሀፍትንና የኮምፒዉተርና ኤሌክትሮኒክስ ተጠቃሚዎችን ታስራለች ሲል ፍሪደም ሀውስ በሪፖርቱ ከሷል። የዋሽንግተን ዲሲው ዘጋቢያችን ናትናኤል ወልዴ ተጨማሪ ዘገባ ልኮልናል።
ናትናኤል ወልዴ
አዜብ ታደሰ
ነጋሽ መሃመድ