የኢኦተ ቤተ ክርስቲያን አባቶች ሽምግልና መክሸፍ፣ 9 ጥር 2005ሐሙስ፣ ጥር 9 2005የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ-ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖደስ 4ኛውን ፓትርያርክ ብፁእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስን ከነሙሉ ሥልጣናቸው ላለመቀበል መወሰኑ እንዳሳዘነው በስደት የሚገኘው ቅዱስ ሲኖደስ ገለጠ። የዋሽንግተኑ ዘጋቢአችን አበበ ፈለቀ ያነጋገራቸውማገናኛዉን ኮፒ አድርግምስል APማስታወቂያ የሲኖዶሱ ዋና ጸሐፊ፣ ብፁእ አቡነ መልክ ጸዴቅ ፣ ሲኖዶሱ፣ ከዚህ በኋላ ፣ ሰሜን አሜሪካ ውስጥ ነጻና ገለልተኛ የሆነ ሲኖዶስ ለማቋቋም ወስኗል ሲሉ ገልጸዋል። 2 ቱን ሲኖዶሶች ለማስታረቅ ሲንቀሳቀስ የነበረው፤ የሰላምና ዕርቅ ኮሚቴም ፤ ትናንት ከአዲስ አበባ የተላለፈው ውሳኔ የሰላም ጥረቱን እንደሚያደናቅፈው ጠቁሟል። አበበ ፈለቀ አርያም ተክሌ