1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢጣሊያ ጦር ዘመቻና የማርሻል ኢፍጣር ትዕዛዝ

ሐሙስ፣ ሐምሌ 27 2009

የማርሻሉ ማስጠንቀቂያ የተሰማዉ፤ ስደተኛ አሸጋጋሪዎችን ታድናለች የተባለች አንዲት የኢጣሊያ ቃኚ ጀልባ ባካባቢዉ ሊቢያ ጠረፍ ከደረሰች በኋላ ነዉ።የቀድሞዉ የሊቢያ ቅኝ ገዢ ኢጣሊያ ሊቢያ ዉስጥ የሚንቀሳቀሱ ስደተኛ አሸጋጋሪዎችን የሚያድን ጦር እንድታዘምት የሐገሪቱ ምክር ቤት ትናንት ወስኗል።

Migration Rettung von Flüchtlingen im Mittelmeer
ምስል picture-alliance/dpa/A. Surinyach

የኢጣሊያ ዘመቻና የኢፍጣር ማስጠንቀቂያ

This browser does not support the audio element.

ምሥራቃዊ ሊቢያን የሚቆጣጠረዉ ጦር አዛዥ ኸሊፋ ሐፍጣር ወደ ሊቢያ የባሕር ክልል ያለፍቃድ የሚገባ የዉጪ ጦርን እንደሚመቱ አስጠነቀቁ።ለራሳቸዉ የፊልድ ማርሻል ማዕረግ ያጠለቁት ሐፍጣር ዛሬ እንዳስታወቁት ጦራቸዉ በራስ ላኑፍ፤ጡብሩክ እና በትሪፖሊ በኩል የሚገባ የዉጪ ጦርን እንዲመታ ታዝዟል።የማርሻሉ ማስጠንቀቂያ የተሰማዉ፤ ስደተኛ አሸጋጋሪዎችን ታድናለች የተባለች አንዲት የኢጣሊያ ቃኚ ጀልባ ባካባቢዉ ሊቢያ ጠረፍ ከደረሰች በኋላ ነዉ።የቀድሞዉ የሊቢያ ቅኝ ገዢ ኢጣሊያ ሊቢያ ዉስጥ የሚንቀሳቀሱ ስደተኛ አሸጋጋሪዎችን የሚያድን ጦር እንድታዘምት የሐገሪቱ ምክር ቤት ትናንት ወስኗል።ሥለዘመቻዉ ዉሳኔና ዓላማ የሮም ወኪላችን ተኽለእግዚ ገብረየሱስን በስልክ አነጋግሬዋለሁ።

ተኽለእዝጊ ገብረእየሱስ

ነጋሽ መሐመድ

አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW