ኤርትራ የመዋዕለ ነዋይ መስሕብ አላት
ማክሰኞ፣ ሐምሌ 3 2010![Frankreich Paris Hanna Simon, Botschafterin Eritrea](https://static.dw.com/image/44606294_800.webp)
ማስታወቂያ
በአፍሪቃ ቀንድ በተለይም በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካካል የተጀመረዉ መቀራረብ እና ሠላማዊ ግንኙነት የዉጪ ባለሐብቶች ኤርትራ ዉስጥ መዋዕለ ነዋያቸዉን ሥራ ላይ እንዲያዉሉ የሚያበረታታ መሆኑን በፈረንሳይ የኤርትራ አምባሳደር አስታወቁ።አምባሳደር ሐና ስምዖን የማንዴላ ተቋም ባዘጋጀዉ ኢንቨስትመንት በአፍሪቃ በተሰኘዉ ስብሰባ ላይ እንዳሉት ኤርትራ የዉጪ ባለሐብቶች ሊወርቱባቸዉ የሚችሉ በርካታ መስሕቦች አሏት።ሥልታዊ አቀማመጥዋም የዉጪ ባለሐብቶች እንዲወርቱባት የሚረዳ ነዉ።የፓሪሷ ወኪላችን ኃይማኖት ጥሩነሕ ዝርዝር ዘገባ ልካልናለች።
ሐይማኖት ጥሩነሕ
ነጋሽ መሐመድ
ኂሩት መለሰ