1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል
ፖለቲካየመካከለኛው ምሥራቅ

የእሥራኤል ፍልስጥኤም ደም አፋሳሹ ግጭት ቀጥሏል

ረቡዕ፣ ሰኔ 14 2015

የእሥራኤል ፍልስጥኤም ግጭት ካለፈው ሰኞ ጀምሮ ምዕራብ ዮርዳኖስ ውስጥ እጅግ ተባብሶ ቀጥሏል ። በሁለቱም በኩል የሰላማዊ ሰዎች ሕይወት እንዲቀጠፍም ሰበብ ሆኗል ። ዳግም ስላገረሸው የእሥራኤል ፍልስጥኤም ግጭት ሰበብ እና አንደምታውን በተመለከተ የተደረገ ቃለ መጠይቅ ።

Westjordanland | Israelischer Militäreinsatz in Jenin
ምስል Nedal Eshtayah/AA/picture alliance

ያገረሸው ግጭት እጅግ እንዳይባባስ አሥግቷል

This browser does not support the audio element.

ሄድ መለስ የሚለው የእሥራኤል እና የፍልስጥኤም ግጭት ዳግም በምዕራብ ዮርዳኖስ ከሰሞኑ ጠንከር ብሎ አገርሽቷል ። የእሥራኤል መከላከያ ሠራዊት አራት እሥራኤላውያን የገደሉ የፍልስጥኤም ታጣቂዎችን ቤት ለማፍረስ በሚል በኃይል በተያዘችው ምዕራብ ዮርዳኖስ ተጨማሪ ኃይል ዛሬ መላኩ ተዘግቧል ። የእሥራኤል መንግሥት ጥቃቱን ያደረሱት «ከሐማስ ጋር ግንኙነት ያላቸው ታጣቂዎች» ናቸው ብሏል ። ግድያው ትናንት የተፈጸመው ጄኒን ከተማ ውስጥ ሰባት ፍልስጥኤማውያን በጄኒን የስደተኞች መጠለያ ውስጥ በእሥራኤል ወታደሮች ጥቃት ከተገደሉ ከአንድ ቀን በኋላ ነው ።  

ምዕራብ ዮርዳኖስ፤ የእሥራኤል ጦር ጄኒን ውስጥ ጥቃት ካደረሰበት ሥፍራ በወታደራዊ ተሽከርካሪዎች ሲወጣ የፍልስጥኤማውያን ጓዳ ሠራሽ ፈንጂ በአጠገቡ ፈንድቶምስል Nedal Eshtayah/AA/picture alliance

ምዕራብ ዮርዳኖስ ውስጥ በሚገኘው የኤሊ ሠፈራ መንደር የተገደሉት እሥራኤላውያን ከ64 ዓመቱ አዛውንት በስተቀር ሦስቱ ዕድሜያቸው ከ21 ዓመት በታች ነው ተብሏል ። በሔሊኮፕተር ጭምር የታገዘው የእሥራኤል ጦር ምዕራብ ዮርዳኖስ ጄኒን የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ላይ ባደረሰው ጥቃት ከተገደሉት ፍልስጥኤማውያን ወጣቶች መካከል ደግሞ የ15 ዓመት ታዳጊም ይገኝበታል ተብሏል ። በጥቃቱ 91 ፍልስጥኤማውያን መቁሰላቸውም ተዘግቧል ። የጄኒን የስደተኞች መጠለያ የተመሰረተው እንደ ጎርጎሪዮስ አቆጣጠር በ1953 ነው ።

ብርቱው ደም አፋሳሽ ግጭት የተቀሰቀሰው የእሥራኤል ጦር ሰኞ ሰኔ 12 ቀን፣ 2015 ዓ.ም ማለዳ የፍልስጥኤም ጄኒን የስደተኞች መጠለያ ጣቢያን ድንገት በመውረር ጥቃት ካደረሰ በኋላ ነው ተብሏል ።  የእሥራኤል ጦር የስደተኛ ጣቢያውን ወርሮ ጥቃት ያደረሰው ሁለት «ተጠርጣሪ ታጣቂ» ፍልስጥኤማውያንን በቁጥጥር ስር ለማዋል ነው ብሏል ። ከተጠርጣሪዎቹ መካከል አንደኛው ከስድስት ወር በፊት ከእስር የተለቀቁት የቀድሞው የፍልስጥኤም እስረኛ ዓሰም አቡ አል ሐይጃ ይገኙበታል ተብሏል ። 

የእሥራኤል ፍልስጥኤም ግጭት ዳግም ያገረሸባት ምዕራብ ዮርዳኖስምስል Majdi Mohammed/AP Photo/picture alliance

የተባባሰው ደም አፋሳሽ ግጭትን ተከትሎ የእሥራኤል ቀኝ አክራሪ መንግሥት በምዕራብ ዮርዳኖስ መጠነ ሰፊ ዘመቻ እንዳይከፍትም አስግቷል ። አንዳንዶች ከወዲሁ ጥሪውን እያስተላለፉ መሆኑም ተሰምቷል ። የግጭቱ መቀስቀስ ሰበብ እና አንደምታውን በተመለከተ በእሥራኤል እየሩሳሌም የመካከለኛው ምሥራቅ የዶይቸ ቬለ ዘጋቢ ዜናነህ መኮንን ማብራሪያ ሰጥቷል ። 

ቃለ መጠይቁን ከድምፁ ማእቀፍ ማድመጥ ይቻላል

ማንተጋፍቶት ስለሺ

ዜናነህ መኮንን

እሸቴ በቀለ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW

ተጨማሪ መረጃ ከ DW