የእስረኞች መፈታትና የአዉሮጳ ኅብረት ምላሽ
ዓርብ፣ የካቲት 2 2010ማስታወቂያ
የአውሮጳ ህብረት የኢትዮጵያ መንግሥት እስረኞችን በይቅርታ ለመልቀቅ መወሰኑን አዎንታዊ እርምጃ ሲል አወደሰ። በኢትዮጵያ የሚካሄደውን የፖለቲካ ተሀድሶንም እንደሚደግፍ አስታወቀ። የህብረቱ ቃል አቀባይ ካትሪን ሬይ ዛሬ ለዶቼቬለ በሰጡት አስተያየት ባለፉት ሳምንታት በሺህዎች የሚቆጠሩ እሥረኞች መፈታታቸው እንዲሁም ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ አንዷለም አራጌን ጨምሮ ሌሎችንም ታራሚዎች ለመፍታት መወሰኑ ትክክለኛ አቅጣጫን የሚያሳይ እርምጃ ነው ብለዋል ከዚሁ ጎን ለጎን የተቃዋሚ ሰልፈኞችን ጥያቄዎችም በውይይት እንዲፈታ አሳስበዋል።
ገበያዉ ንጉሴ
አዜብ ታደሰ
ኂሩት መለሰ