የእነ አቶ ምትኩ በየነ የፍርድ ቤት ውሎ
ሰኞ፣ የካቲት 11 2011ማስታወቂያ
አቶ ምትኩ በጠየቁት የዋስትና ጥያቄ ላይና ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በጠየቀው ተጨማሪ ቀን ላይ ውሳኔ ለመስጠት ፍርድ ቤቱ ለነገ የቀጠረ ሲሆን በሌሎች ተጠርጣሪዎች ላይ 10 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
የባሕር ዳርና አካባቢው ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዛሬ ከሰአት በፊት መጀመሪ የተመለከተው ላፓል የሚባል ካምፓኒ ባለቤት ሆነው ሲሰሩ ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ ከጥረት ኮርፖሬት ጋር በመመሳጠር የህዝብ ገንዘብ አባክነዋል ባላቸው በእነወ/ሮ አይናለም ኃይለ ልኡልና በሁለት ሴት ልጆቻቸው መዝገብ የተከፈተውን የምርመራ መዝገብ ነው፡፡ የአማራ ክልል ስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን መርማሪ ቡድን ባለፉት ቀጠሮ በተሰጠባቸው 14 ቀናት ያከናወነውን ተግባራት ለፍርድ ቤቱ በዝርዝር አቅርቧል፡፡
ሆኖም አንዳንድ የሰነድ ማስረጃዎችን በቀላሉ ማግኘት አልቻልኩም፣ የሰው ምስክሮች አካባቢውን የለቀቁና በተበታተነ ሁኔታ ስለሚገኙ መረጃዎችን አጠናቅቄ አልጨረስኩም በመሆኑም ተጨማሪ 14 ቀን የምርመራ ጊዜ ፈቀድልኝ ሲል ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።
ዓለምነው መኮንን
እሸቴ በቀለ
ሸዋዬ ለገሠ