1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የእነ አቶ ምትኩ በየነ የፍርድ ቤት ውሎ 

ሰኞ፣ የካቲት 11 2011

ከጥረት ኮርፖሬሽን ጋር በተያዘ ተጠርጥረው ጉዳቸው እየተጣራ ያለው የእነ አቶ ምትኩ በየነ የምርመራ ሂደት ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ መታየት ጀምሯል፡፡ አቶ ምትኩ በጠየቁት የዋስትና ጥያቄ ላይና ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በጠየቀው ተጨማሪ ቀን ላይ ውሳኔ ለመስጠት ፍርድ ቤቱ ለነገ ተቀጥሯል

Äthiopien Mitiku Beyene
ምስል DW/A. Mekonnen

የእነ አቶ ምትኩ በየነ የፍርድ ቤት ውሎ 

This browser does not support the audio element.

አቶ ምትኩ በጠየቁት የዋስትና ጥያቄ ላይና ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በጠየቀው ተጨማሪ ቀን ላይ ውሳኔ ለመስጠት ፍርድ ቤቱ ለነገ የቀጠረ ሲሆን በሌሎች ተጠርጣሪዎች ላይ 10 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል፡፡

የባሕር ዳርና አካባቢው ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዛሬ ከሰአት በፊት መጀመሪ የተመለከተው ላፓል የሚባል ካምፓኒ ባለቤት ሆነው ሲሰሩ ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ ከጥረት ኮርፖሬት ጋር በመመሳጠር የህዝብ ገንዘብ አባክነዋል ባላቸው በእነወ/ሮ አይናለም ኃይለ ልኡልና በሁለት ሴት ልጆቻቸው መዝገብ የተከፈተውን የምርመራ መዝገብ ነው፡፡ የአማራ ክልል ስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን መርማሪ ቡድን ባለፉት ቀጠሮ በተሰጠባቸው 14 ቀናት ያከናወነውን ተግባራት ለፍርድ ቤቱ በዝርዝር አቅርቧል፡፡
ሆኖም አንዳንድ የሰነድ ማስረጃዎችን በቀላሉ ማግኘት አልቻልኩም፣ የሰው ምስክሮች አካባቢውን የለቀቁና በተበታተነ ሁኔታ ስለሚገኙ መረጃዎችን አጠናቅቄ አልጨረስኩም በመሆኑም ተጨማሪ 14 ቀን የምርመራ ጊዜ ፈቀድልኝ ሲል ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።


ዓለምነው መኮንን


እሸቴ በቀለ
ሸዋዬ ለገሠ

 

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ የ DW ታላቅ ዘገባ

የ DW ታላቅ ዘገባ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ከ DW