የእንግሊዝ ባንክና የሶማሊያ የገንዘብ መለወጫ
ረቡዕ፣ ጥቅምት 27 2006ማስታወቂያ
ባንኩ ይህን የወሰነዉ በባንኩ የሚላከዉ ገንዘብ ለአሸባሪዎች መጠቀሚያ ይዉላል ከሚል ጥርጣሬ እንደሆነ ተገልጿል። ዘገባዎች እንደሚሉት ሶማሊያ ከአሜሪካ የሚሰጣትን የርዳታ ገንዘብ መጠን ያህል ገቢ በቀሪዉ ዓለም ከተበተኑት ከገዛ ዜጎቿ ታገኛለች። የተጠናከረ የመንግስት መዋቅርና የባንክ ስርዓት በሌለበት ይህን ያህል ገቢ የምታገኘዉ ጦርነት እና ግጭት ያመሳቀላት ሀገር የባርክሌ ባንክ ዉሳኔ ሊጎዳት እንደሚችል ነዉ የሚገመተዉ። ሕጋዊዉ የገንዘብ ማሸጋገሪያ መንገድ መስተጓጎል ለሕገወጥ የገንዘብ ዝዉዉር መንገድ ይከፍታል የሚሉ ወገኖች አሉ። ሆኖም ባንኩ ትናንት አዲስ ሃሳብ ብልጭ አድርጓል። ዝርዝሩን ከድምፅ ዘገባዉ ያድምጡ።
ሃና ደምሴ
ሸዋዬ ለገሠ